የቡሩንዲ ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሩሲያን የሕግ አውጪ ምክር ቤት ምርጫ ለመታዘብ ወደ ሩሲያ ተጓዙ
10:15 17.09.2026 (የተሻሻለ: 10:24 17.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቡሩንዲ ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሩሲያን የሕግ አውጪ ምክር ቤት ምርጫ ለመታዘብ ወደ ሩሲያ ተጓዙ
ጉብኝቱ በሩሲያ ባለሥልጣናት ጥሪ እንደሚካሄድ ጄላስ ዳንኤል ንዳቢራቤ ከጉዟቸው በፊት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጸዋል።
የሩሲያ ታዛቢዎች በሰኔ ወር ለብሩንዲ ሕግ አውጭ ምክር ቤት ምርጫ ወደ ሀገሪቱ መጥተው እንደነበር አስታውሰዋል።
የጉዞው ሌላ ዓላማ፤ “ወዳጅነትን ማጠናከር” እና “የፓርላማ ዲፕሎማሲን” በተግባር ማዋል ነው ብለዋል።
የሩሲያ የሕግ አውጭ ምክር ቤት ምርጫ ከመስከረም 8 እስከ 10 ይካሄዳል። ምርጫው የታችኛው የፓርላማ ምክር ቤት (ስቴት ዱማ) 450 መቀመጫዎችን የሚያድስ ይሆናል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X