የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በዓለም ወጣቶች ፌስቲቫል ላይ በምዕራባውያን፣ በዩክሬን እና በብዝኃ-ዋልታ ዓለም ላይ የሩሲያን ስትራቴጂያዊ ራዕይ አብራሩ

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በዓለም ወጣቶች ፌስቲቫል ላይ በምዕራባውያን፣ በዩክሬን እና በብዝኃ-ዋልታ ዓለም ላይ የሩሲያን ስትራቴጂያዊ ራዕይ አብራሩ
ሰርጌ ላቭሮቭ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ፦
ከምዕራባውያን ጋር ያለውን ግንኙነት በተመለከተ
ምዕራባውያን የባለብዙ-ዋልታ ዓለም አቀፍ ሥርዓት መፈጠርን ለታሪካዊ የበላይነታቸው እንደ ስጋት ይመለከቱታል።
በሩሲያ ላይ ስትራቴጂያዊ ሽንፈትን ማድረስ የምዕራባውያን ዋነኛ ምኞት ሆኖ ቀጥሏል።
ሩሲያ በ1990ዎቹ አድርጋው እንደነበረው ወደ አውሮፓ ፖለቲካዊ እቅፍ አትመለስም።
ሞስኮ የራሷን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ስምምነቶችን ከአውሮፓ ሀገራት ጋር አትፈራረም።
ሩሲያ የዶላርን ዓለም አቀፍ ሚና አላዳከመችም፤ ነገር ግን ከአጋሮቿ ጋር አዳዲስ የክፍያ ስልቶችን ለመዘርጋት ተገዳለች።
ሩሲያ አውሮፓን የማጠቃት እቅድ የላትም፤ ነገር ግን ማንኛውም የአውሮፓ ወረራ እጅግ አጭር ወደሆነ ጦርነት እንደሚመራ አስጠንቅቃለች።
ላቭሮቭ አውሮፓ አጭር ስለሚሆነው ጦርነት የተሰጠውን ይህንን ማስጠንቀቂያ ሰምታዋለች የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።
ማንኛዋም የአውሮፓ ሀገር ውይይት ለመቀጠል ፍላጎት ካላት፣ ሩሲያ ሀሳቧን ለመስማት ዝግጁ ናት።
የዩክሬን ግጭት እልባት
አውሮፓ በዩክሬን ሥልጣን ላይ ያለውን የናዚ እና ሩሲያ-ጠል ስርዓት አስጠብቆ ለማቆየት እና በቁጥጥር ስር ባሉ ግዛቶች ውስጥ ጦር ለማሰማራት ትፈልጋለች።
ዘላቂ መፍትሔ ለማግኘት የልዩ ወታደራዊ ዘመቻውን የመጀመሪያ ዓላማዎች ማሳካት እና የግጭቱን መነሻ መንስኤዎች ማስወገድ ያስፈልጋል።
ሩሲያ ለሁለትዮሽ ወይም ለሦስትዮሽ ድርድሮች ዝግጁ ሆና የምትቀጥል ሲሆን አዳዲስ ሐሳቦችንም ትጠብቃለች፤ ሆኖም ከፍ ያለ ተስፋ የላትም።
ብሪክስ እና ዓለም አቀፍ አጋርነቶች
የብሪክስ ስብስብ ለአዳዲስ አባል ሀገራት ተሳትፎ ክፍት ሆኖ ይቀጥላል።
ሩሲያ እና ኡጋንዳ ካላቸው ጠንካራ ፖለቲካዊ አጋርነት ጋር የሚመጣጠን የኢኮኖሚ ግንኙነታቸውን በንቃት እያሰፉ ይገኛሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X