ዛሬ እየተገበርነው ያለው በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ ናቸው - ዐቢይ አሕመድ

ሰብስክራይብ

ዛሬ እየተገበርነው ያለው በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ ናቸው - ዐቢይ አሕመድ

ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አዲሱን የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መጀመር አስመልቶ ለተማሪዎች እና ለመምህራን ባስተላለፉት የማኅበራዊ ሚዲያ መልዕክት ላይ ገልጸዋል፡፡

"እያንዳንዱ ተማሪ ለላቀ እውቀት በትጋትና ጉጉት ትምህርቱን እንዲከታተል፣ ለጥሩ ውጤት በጽናት እንዲተጋ፣ እንዲሁም የሀገራችንን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች እንዲገነባ አበረታታለሁ።"

መጪውን ዘመን ታሳቢ ያደረጉ ልማቶች ተጠቃሚ እና ባለአደራ የሆነው ትውልድ፣ የኢትዮጵያን ታላቅ የሥልጣኔ ታሪክ ወደፊት የማስቀጠል ቁርጠኝነቱ መሠረት እንደሆነ ሙሉ እምነታቸው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

መምህራንም ተማሪዎችን የማነቃቃት፣ አቅማቸውን የመግለጥ፣ እንዲሁም ለነገ ተፎካካሪ የሚያደርጋቸውን እውቀት፣ ክህሎትና እሴቶች የማስታጠቅ አደራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0