ነጭ የደቡብ አፍሪካ ስደተኞች ከትራምፕ የመልሶ ማቋቋም ቃል ኪዳን በኋላ ሃሳቡ ውድቅ መደረጉ በደብዳቤ እንደተገለፀላቸው ተዘገበ
10:46 16.09.2026 (የተሻሻለ: 10:54 16.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ነጭ የደቡብ አፍሪካ ስደተኞች ከትራምፕ የመልሶ ማቋቋም ቃል ኪዳን በኋላ ሃሳቡ ውድቅ መደረጉ በደብዳቤ እንደተገለፀላቸው ተዘገበ
እንደ ሚዲያ ዘገባዎች፣ አፍሪካነርስ ለተባሉት የደቡብ አፍሪካ ነጭ ዜጎች የስደተኝነት መብት የሚሰጠው ፕሬዝዳንት ትራምፕ እ.ኤ.አ. በየካቲት 2025 ያስተላለፉትን ትእዛዝ ተከትሎ ከ13 ሺህ በላይ ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን ወደ አሜሪካ ተንቀሳቅሰዋል።
ሆኖም ግን፣ በደርዘን የሚቆጠሩ አመልካቾች "ለቀጣይ ሂደት ብቁ አይደላችሁም" የሚሉ እና ውሳኔውም "ይግባኝ ሊባልበት የማይችል" መሆኑን የሚገልጹ ጥያቄአቸው ውድቅ የተደረገባቸው ደብዳቤዎች እየደረሷቸው ይገኛል።
የአሜሪካ የዜግነት እና የኢሚግሬሽን አገልግሎት ስለ አጠቃላይ የስደተኞች ማመልከቻዎችም ሆነ ውድቅ ስለተደረጉት መረጃ ስላላወጣ ውድቅ የተደረጉት አመልካቾች ትክክለኛ ቁጥር እስካሁን ግልጽ እንዳልሆነ ዘገባዎቹ አሳይተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X