አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 38 ቢሊዮን ዶላር አውድማለች፤ የሚሳኤል መከላከያዋ እየተሟጠጠ ነው - የአሜሪካ የበጀት ተቆጣጣሪ

አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 38 ቢሊዮን ዶላር አውድማለች፤ የሚሳኤል መከላከያዋ እየተሟጠጠ ነው - የአሜሪካ የበጀት ተቆጣጣሪ
አዲሱ የኮንግረስ የበጀት ቢሮ ሪፖርት እንዳመለከተው፣ የአሜሪካ ፔንታጎን ከኢራን ጋር ባደረገው ጦርነት እስከ ሐምሌ 25 (ኦገስት 1) ድረስ በግምት 38.1 ቢሊዮን ዶላር ወጪ አድርጓል። ሂሳቡም አሁንም እየጨመረ ይገኛል። የበጀት ቢሮው አክሎም፣ እንደ ውጊያው ጥንካሬ ተጨማሪ የአንድ ወር ውጊያ ከ2 እስከ 3 ቢሊዮን ዶላር ሊያስወጣ ይችላል።
ትልቁን ወጪ የወሰደው የጦር መሣሪያ አቅርቦት ነው። አሜሪካ ቀደም ሲል ጥቅም ላይ የዋሉ መሣሪያዎችን ለመተካት በግምት 21.7 ቢሊዮን ዶላር ያወጣች ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 13.1 ቢሊዮን ዶላር በኢራን ባሊስቲክ ሚሳኤሎች እና ድሮኖች ላይ ጥቅም ላይ የዋሉትን የሚሳኤል-መከላከያ አክሻፊዎችን ለመተካት ውሏል።
አሜሪካ እ.ኤ.አ. ከሰኔ 2025 ጀምሮ ከነበራት የሮኬት መከላከያ ሚሳኤሎች ክምችት ውስጥ "ከግማሽ እስከ ሁለት ሦስተኛ የሚሆነውን" የተጠቀመች ሲሆን፣ የኢራን ጦርነት ደግሞ ይህን ክምችት የበለጠ እንዲያሽቆለቁል አድርጎታል። ምርቱ ቢጨምር እንኳ እነዚህን ክምችቶች መልሶ ለመተካት ቢያንስ አምስት ዓመታት ይወስዳል።
ኢራንም በበኩሏ ከፍተኛ የመሣሪያ ውድመት አድርሳለች። የበጀት ቢሮው እንደገለጸው፣ የውጊያ ውድመቱ መጠን በግምት 1.9 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ይህም የ500 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያለውን የ"ትሃድ" ራዳር፣ አውሮፕላኖች እና ድሮኖችን ያካትታል።
የዚህ ግጭት ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖ አሜሪካውያንንም እየጎዳ ይገኛል። ግጭቱ የነዳጅ፣ የጋዞሊን እና የናፍጣ ዋጋ እንዲንር በማድረግ ለዋጋ ንረት አስተዋጽኦ ያደረገ ሲሆን፣ የነዳጅ ዋጋ መጨመርም ወደ አጠቃላይ ኢኮኖሚው እየተሸጋገረ ይገኛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X