የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክን ማጠናከር ይገባል – ኢትዮጵያዊ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክን ማጠናከር ይገባል – ኢትዮጵያዊ ባለሙያ

 

በኒው ዴልሂ በተካሄደውን የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ ላይ በዓለም አቀፍ ተቋማት ውስጥ ያለው ውክልና እና የድምፅ አሰጣጥ ሥልጣን አሳሳቢ ሆኖ የተነሳ ጉዳይ እንደነበር የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ መምህር ሙሉዓለም ኃይለማርያም ጉባኤውን አስመልክቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት አስተያየት አስታውሰዋል፡፡

 

“ሌላው አስፈላጊ ነጥብ አማራጮችን መገንባት ሲሆን፣ እሱም እንደ ብሪክስ አዲስ ልማት ባንክ የመሳሰሉ ተቋማትን ማጠናከር ነው። አማራጭ የክፍያ ዝግጅቶች እና አዲስ የልማት ፋይናንሲንግ ስልቶችም እንዲሁ አስፈላጊ ናቸው።” ብለዋል፡፡

 

እነዚህ የታቀዱ ማሻሻያዎች እና አማራጭ የፋይናንስ ሥርዓቶች የዓለም አቀፍ ኢኮኖሚን የኃይል ሚዛን በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖራቸው ባለሙያው አስረድተዋል፡፡

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0