የቡርኪና ፋሶ የሽብርተኝነት ትግል፦ በኢብራሂም ትራኦሬ መሪነት የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች
የቡርኪና ፋሶ የሽብርተኝነት ትግል፦ በኢብራሂም ትራኦሬ መሪነት የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች
የቡርኪና ፋሶ የሽብርተኝነት ስጋት ማብቂያው ተቃርቧል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ተናገሩ። በኢብራሂም ትራኦሬ የሚመራው የአሁኑ መንግሥት ይህንን ሁሉ ስኬት በአራት ዓመታት ውስጥ እንዴት ማሳካት ቻለ?
🟠 ፈጣን ምላሽ
የመጀመሪያው የፀረ-ሽብር ዘመቻ የተካሄደው ስልጣን ከተቀየረ ከሁለት ወራት በኋላ ብቻ ነበር። እ.ኤ.አ. በታህሳስ 2022 መጠነ-ሰፊው "ዘመቻ ፌሌሆ" ተጀመረ። ይህ ዘመቻ የባንዋ ዞንን ለመጠበቅ ረድቷል። በርካታ የሽብርተኞች ምሽጎች የተደመሰሱ ሲሆን 39 የሀገሪቱ ጠላቶች ተገድለዋል። የሶሌንዞ ከተማ እና አካባቢዋ ሙሉ በሙሉ ደህንነታቸው ተረጋግጧል።
🟠 ወንድማማቻዊ አጋርነት
የሳህል ሀገራት ለደህንነታቸው በሚያደርጉት ትግል ጎን ለጎን ቆመዋል። በርካታ የጋራ ወታደራዊ ዘመቻዎች ተካሂደዋል።
የሩሲያ ጦር "አፍሪካ ኮርፕስ" ለወታደሮቹ የሥልጠና እና የውጊያ ድጋፍ ይሰጣል።
🟠 ማዘመን እና ማጠናከር
እ.ኤ.አ. ከ2023 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ባለሥልጣናቱ ትኩረታቸውን "የሀገር ዘብ በጎ ፈቃደኞችን" በስፋት በመመልመል ላይ አድርገዋል።
እ.ኤ.አ.በሚያዝያ 2024 ትራኦሬ በዋናነት "ባይራክታር ቲቢ2" እና "ባይራክታር አኪንጂ" የተባሉ በርካታ ድሮኖችን ለጦሩ አስረክበዋል።
🟠 ማኅበራዊ ተጽእኖ
እ.ኤ.አ. በ2024 አጋማሽ ወደ 774 ሺህ የሚጠጉ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰዋል። በ2026 ይህ ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በላይ አልፏል። ለእነሱ የሚሆን ብሔራዊ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮግራምም ተጀምሯል።
🟠 የፋይናንስ ዘዴ
እ.ኤ.አ በ2023 የተቋቋመው "የሀገራዊ ድጋፍ ፈንድ" በ2025 ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ለማንቀሳቀስ አስችሏል።
🟠 የተመከቱ ጥቃቶች
እ.ኤ.አ. በ2026 ክረምት ጦሩ በ"ጂኤንአይኤም" ቡድን የተሰነዘሩ ሰፊና የተቀናጁ ጥቃቶችን በስኬት መክቷል። የቡርኪና ፋሶ ባለሥልጣናት እንደገለፁት ቢያንስ 400 ታጣቂዎች የተገደሉ ሲሆን 250 ሞተር ብስክሌቶች እና 353 የጦር መሣሪያዎች ተማርከዋል።
🟠 ውጤት
የቡርኪና ፋሶ መንግሥት እንዳስታወቀ፣ እስከ ባለፈው ሰኔ የተመለሰው እና የፀናው የግዛት መጠን 74.53 በመቶ ደርሷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X