ሩሲያ ባለፈው ሌሊት በዩክሬን የሎጂስቲክስ ማዕከላት ላይ ጥቃት ፈጸመች
17:55 15.09.2026 (የተሻሻለ: 18:04 15.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ ባለፈው ሌሊት በዩክሬን የሎጂስቲክስ ማዕከላት ላይ ጥቃት ፈጸመች
የሩሲያ ኃይሎች ለዩክሬን ጦር አቅርቦት በሚውሉ የሎጂስቲክስ ማዕከላት፣ ወደቦች እና የጭነት መርከቦች ላይ ያነጣጠረ የድሮን ጥቃት ፈጽመዋል።
በኦዴሳ ክልል - ከውጭ ሀገራት የሚገቡ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለማከማቸት እና ለማሰራጨት በሚያውለው በቬሊካያ ባልካ በሚገኝ የሎጂስቲክስ ማዕከል ላይ፤
በቸርኖሞርስክ ወደብ - ለዩክሬን ጦር አቅርቦቶችን ጭነው በነበሩ የጭነት መርከብ እና የሮ-ሮ ጀልባ ላይ
በምዕራብ ዩክሬን - ከአውሮፓ ሕብረት ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ በሚያውለው የባቡር መስመር መሰረተ ልማት ላይ የተሰነዘረው ጥቃት ቀጥሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X