የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ ፕሬዝዳንት ሊመርጥ ነው
11:43 15.09.2026 (የተሻሻለ: 11:44 15.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ ፕሬዝዳንት ሊመርጥ ነው
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 18ኛ መደበኛ እና የምርጫ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄድ መጀመሩን የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግቧል።
የስብሰባው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ፌዴሬሽኑን ለቀጣዮቹ 4 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት የሚመራውን ግለሰብ ይመረጣል፡፡
ላለፉት 8 ዓመታት ፌዴሬሽኑን በፕሬዝዳንትነት የመሩት ኢሳያስ ጂራ ለቦታው ብቸኛ እጩ ሆነው ቀርበዋል።
በጉባኤው የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጂራ፣ የዋሊያዎቹ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ፣ የክልልና የከተማ ፌዴሬሽን እንዲሁም የክለብ አመራሮች፣ የኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የሊግ አክሲዮን ማኅበር ኃላፊዎች፣ የቀድሞ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች እና የስፖርት ሳይንስ ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡
በስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ የተቀረጸ ቪዲዮ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X