የዩክሬን የነዳጅ ክምችት እና የጦር ኃይል በሩሲያ ኢላማ ተኮር ጥቃቶች ተዳክሟል - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopiaየዩክሬን የነዳጅ ክምችት እና የጦር ኃይል በሩሲያ ኢላማ ተኮር ጥቃቶች ተዳክሟል - ባለሙያ
የዩክሬን የነዳጅ ክምችት እና የጦር ኃይል በሩሲያ ኢላማ ተኮር ጥቃቶች ተዳክሟል - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.09.2026
ሰብስክራይብ

የዩክሬን የነዳጅ ክምችት እና የጦር ኃይል በሩሲያ ኢላማ ተኮር ጥቃቶች ተዳክሟል - ባለሙያ

​የዩክሬይን የአየር መከላከያ አቅም ቢበዛ በ5 በመቶ ብቻ እየሠራ በሚገኝበት ሁኔታ፣ ሩሲያ የሀገሪቱን የጦር ኃይል አቅም፣ መሠረተ ልማት እና ሎጂስቲክስ እንዳታዳክም ለመግታት የምታደርገው ጥረት አነስተኛ መሆኑን ወታደራዊ ጋዜጠኛ አለክሴይ ቦርዜንኮለስፑትኒክ ተናግሯል።

የነዳጅ ማደያዎች በተቀናጀ መንገድ መደምሰሳቸው የዩክሬን ጦር በግንባር ለሚገኙ ወታደሮቹ የሚያደርገውን የነዳጅ አቅርቦት አስተጓጉሎታል። የዩክሬን የጭነት ኮኖቮዮች  መድረሻቸው ሳይደረሱ ነዳጅ እንዳያልቅባቸው የነዳጅ ቦቲዎችን አብረው ለማሰለፍ ተገደዋል፤ ይህም ለሩሲያ ጥቃቶች የበለጠ ተጋላጭ ያደርጋቸዋል።

የዩክሬን ጦር የነዳጅ አቅርቦት መስተጓጎል በግንባር ያሉ የዩክሬን ወታደሮች ጄነሬተሮች ለመሙላት አስቸጋሪ ያደርግባቸዋል፤ ይህም በረዷማው የክረምት ወራት ሲገባ ትልቅ ችግር ይፈጥርባቸዋል።

በዩክሬን የነዳጅ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ተከትሎ በዩክሬን የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ላይ መጠነ-ሰፊ ጥቃቶች ሊከተሉ ይችላሉ፤ ይህም ስትራቴጂካዊ የዩክሬን ከተሞች እና የኢንዱስትሪ ተቋማት ያለ ኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀሩ ሊያደርግ ይችላል።

የሩሲያ ኃይሎች የዩክሬንን የጦር አቅም በማዳከም ላይ ትኩረት በማድረጋቸው፣ በሩሲያ ጥቃቶች እስከ 70 በመቶ የሚደርሱ የዩክሬን የድሮን ማከማቻዎች እና የመገጣጠሚያ ቦታዎች ተደምስሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0