“ወደ ኢትዮጵያ ይምጡ — የ7 ዓመት የእድሜ ቅናሽ ያግኙ” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ሰብስክራይብ

“ወደ ኢትዮጵያ ይምጡ — የ7 ዓመት የእድሜ ቅናሽ ያግኙ” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

በአብዛኛው የዓለም ክፍል ዓመቱ 2026 ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ መስከረም 1 ቀን የ2019 አዲስ ዓመቷን ተቀብላለች ሲሉ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል።

“ለ7 ዓመቱ የእድሜ ቅናሽ ይምጡ፤ ለጥንታዊ ታሪኳ፣ ለተፈጥሮ ድንቆቿ፣ ለታዋቂው ቡናዋ፣ ለማራኪ ምሉዕ ባህሏ እና ለአይረሴ እንግዳ ተቀባይነቷ ይቆዩባት።” ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ፣ ጊዜ ወጣት ሆኖ የሚገኝባት፣ ዘመን አይሽሬ የጉብኝት ዕድሎች ያሏት ሀገር መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኒው ዴልሂ ከተካሄደው የብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት፤ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከኢትዮጵያ ጉብኝት በኋላ "የሰባት ዓመት የዕድሜ ቅናሽ" ተደርጎላቸው እንደተመለሱ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0