የሩሲያው የዓለም የወጣቶች ፌስቲቫል መክፈቻ ለአፍሪካ ልዩ ክብር በመስጠት በደማቅ የባህል ትርኢቶች ተከናወነ - የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ
20:25 13.09.2026 (የተሻሻለ: 20:34 13.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያው የዓለም የወጣቶች ፌስቲቫል መክፈቻ ለአፍሪካ ልዩ ክብር በመስጠት በደማቅ የባህል ትርኢቶች ተከናወነ - የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ
ቭላድሚር ፑቲን ለወጣቶቹ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልእክት ሰላምታ ያቀረቡ ሲሆን፤ "ሚር" የሚለው የሩሲያኛ ቃል "ወዳጅነት" እና "ዓለም" የሚሉ ሁለት ትርጉሞች እንዳሉት እና ይህም በመላው ዓለም በሚኖሩ የብዝኃ-ማንነት መካከል ያለውን የጋራ መከባበር የሚያንጸባርቅ መሆኑን አብራርተዋል።
የሩሲያው ፕሬዝዳንት በመላው ዓለም ለትምህርት፣ ለቴክኖሎጂ እና ለሀብቶች እኩል ተደራሽነት እንዲኖር ጥሪ ማቅረባቸውን የስፑትኒክ ዘጋቢ ገልጿል።
የዓለም የወጣቶች ፌስቲቫል ከመስከረም 1 እስከ 7 በሩሲያዋ የካተሪንበርግ ከተማ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን፤ ከ191 ሀገራት የተወጣጡ ወደ 10 ሺህ ገደማ ተሳታፊዎችን በአንድነት አሰባስቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X