ደቡብ አፍሪካ አዲስ የብሪክስ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቁጥጥር ማዕቀፍ እንዲዘረጋ ሐሳብ አቀርባለች - ራማፎሳ

ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ አዲስ የብሪክስ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቁጥጥር ማዕቀፍ እንዲዘረጋ ሐሳብ አቀርባለች - ራማፎሳ

የሰው ሠራሽ አስተውሎት የሕክምናንና የግብርናን ዘርፎች የመለወጥ እንዲሁም ድህነትን የመቀነስ አቅም ያለው ቢሆንም፣ አልሚዎች ግን እንደ የሳይበር ስጋት፣ የመረጃ አደጋ እና የሰው ልጅ ቁጥጥር ማጣት ያሉ ከባድ ስጋቶች እንዳሉ ያስጠነቅቃሉ ሲሉ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት በኒው ዴልሂ በተካሄደው የብሪክስ+ ጉባኤ ላይ ተናግረዋል።

ከቴክኖሎጂው ዕድገት ጋር እኩል ለመራመድ እንደ አቪዬሽን ወይም የኒውክሌር ኃይል ዘርፎች ሁሉ ጥብቅ የሆነ ውጫዊ ቁጥጥር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ራማፎሳ አሳስበዋል።

ስለሆነም ፕሬዝዳንቱ ብሪክስ የሚከተሉትን ነጥቦች ያካተተ ነፃ የሳይንሳዊ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ግምገማ ሥርዓት መመሥረት እንዳለበት ሃሳብ አቅርበዋል፦

🟠 ትርጉም ያለው የሰው ልጅ ቁጥጥር፣

🟠 አስገዳጅ የሆነ የአደጋ ሪፖርት አቀራረብ፣

🟠 የኤአይ አቅም እያደገ ሲሄድ ጠንካራ የደህንነት ጥበቃዎችን ማድረግ እንዲሁም

🟠 በማደግ ላይ ላሉ ኢኮኖሚዎች በሀገር በቀል የሰው ሠራሽ ሉዓላዊ አቅም ላይ ኢንቨስት ማድረግ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0