በምስራቅ አፍሪካ አረንጓዴ ትራንስፖርት አዲስ ምዕራፍ የሆነው የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች ድንበር ተሻጋሪ ጉዞ
18:15 13.09.2026 (የተሻሻለ: 18:24 13.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በምስራቅ አፍሪካ አረንጓዴ ትራንስፖርት አዲስ ምዕራፍ የሆነው የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች ድንበር ተሻጋሪ ጉዞ
ከኬንያ ናይሮቢ የተነሱ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚንቀሳቀሱ አውቶቡሶች ሞያሌን አቋርጠው ወደ አዲስ አበባ የሚያደርጉትን ታሪካዊ ጉዞ መቀጠላቸውን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ዓላማው፦ ከመስከረም 4-6 በሚካሄደው "የኖርዲክ - አፍሪካ የኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎች ፎረም" የሚሳተፉ እንግዶችን ማጓጓዝ።
ጉዞው፦ ተሳታፊዎቹን ከናይሮቢ–ሞያሌ አድርሰው ወደ አዲስ አበባ ማድረስ፣ እንዲሁም ሲመለሱ ወደ ሞያሌ መሸኘት ነው፡፡
የመሠረተ ልማት እመርታ፦ አውቶቡሶቹ ከአዲስ አበባ 560 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው ያቤሎ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል ቻርጅ ያደርጋሉ።
ትርጉሙ፦ ጉዞው የኢትዮጵያ እና ኬንያን የአረንጓዴ ትራንስፖርት ትስስር እና የቀጣናዊ ውህደት አቅም ያሳያል ተብሏል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia