በኒው ዴልሂ በተካሄደው የብሪክስ ጉባኤ 'ከፍተኛው የአፍሪካውያን ተወካዮች ስብስብ' የተስተዋለበት ሲሆን አኀጉሪቱም የማዕከልነት ስፍራ ይዛለች ተባለ

ሰብስክራይብ

በኒው ዴልሂ በተካሄደው የብሪክስ ጉባኤ 'ከፍተኛው የአፍሪካውያን ተወካዮች ስብስብ' የተስተዋለበት ሲሆን አኀጉሪቱም የማዕከልነት ስፍራ ይዛለች ተባለ

ኒው ዴልሂ ብሪክስን ከጂኦፖለቲካዊ ግጭቶች በማራቅ የሰዎችን ሕይወት በቀጥታ በሚነኩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ያደረገች ሲሆን፣ አፍሪካም በሂደቱ ማዕከላዊ ሚና ተጫውታለች ሲሉ የግሎባል ኢንዲያ ኢንሳይት ማዕከል መሥራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ማኒሽ ቻንድ በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

ከባለሙያው የተሰጡ ዋና ዋና ነጥቦች፦

የአፍሪካ ተወካዮች፦ ደቡብ አፍሪካ ብቻዋን የድርጅቱ አባል ከነበረችበት ጊዜ በተለየ መልኩ፣ አሁን ላይ ኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ኡጋንዳ እና ናይጄሪያ በስብሰባው ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ለብሪክስ አዲስ ትርጉም፦ ሕንድ ለምህፃረ ቃሉ አዲስ ትርጉም የሰጠች ሲሆን፣ BRICS "Building for Resilience, Innovation, Cooperation, and Sustainability" (ፅናት፣ ፈጠራ፣ ትብብር እና ዘላቂነትን መገንባት) የሚል መርህን ይዟል።

ስፋቱን ማሳደግ፦ የኒው ዴልሂው መግለጫ ጤናን፣ ኃይልን፣ አረንጓዴ ኃይልን፣ አዳዲስ ሥራ ፈጠራዎችን፣ የፈጠራ ሥራዎችን፣ ባህልን እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን የሚያቀፉ ከ30 እስከ 40 የሚደርሱ አዳዲስ ጥረቶችን ይዟል።

የሰላም ሃይል፦ በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ላይ ልዩነቶች ቢኖሩም፣ የብሪክስ አባላት ልዩነቶቻቸውን ያጠበቡ ሲሆን፣ መግለጫውም ስለማይነጣጠል ሰላም ይናገራል።

አካታች የዓለም ስርዓት ፦ ብሪክስ በማደግ ላይ ያለችውን የአፍሪካ አኀጉር በሰፊው የብዙ ወገን አጀንዳ ውስጥ በማካተት፣ አካታች እና ተወካይነት ያለው የዓለም ስርዓት በመፍጠር ላይ ትኩረት አድርጓል።

ለተጨማሪ መረጃ ቪዲዮውን ይመልከቱ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0