ዓለም አቀፉ የወጣቶች ፌስቲቫል በሩሲያዋ የካተሪንበርግ ተጀመረ
19:17 12.09.2026 (የተሻሻለ: 19:34 12.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ዓለም አቀፉ የወጣቶች ፌስቲቫል በሩሲያዋ የካተሪንበርግ ተጀመረ
ፌስቲቫሉ በሙያ ልምዳቸው መሠረት ለተመረጡ እንዲሁም በሚኖሩበት ዓለም መጪ ዘመን ተጽዕኖ ለማሳደር በጋራ ዓላማ ለተሰባሰቡ እና በማኅበራዊ ጉዳዮች ንቁ ተሳትፎ ላላቸው ወጣቶች መድረክ ሆኖ ያገለግላል።
ከ6,500 በላይ ተሳታፊዎች ከወዲሁ የደረሱ ሲሆን ተጨማሪ የልዑካን ቡድኖች መግባታቸውን ቀጥለዋል።
ፌስቲቫሉ ለእውነተኛ ውይይት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በጋራ የተሻለ ዓለም ለመገንባት በቆረጡ ወጣቶች መካከል ዘላቂ ትስስር የመፍጠር ዓላማ አንግቧል። ተሳታፊዎቹ ዓለምን ለመለወጥ በሚያደርጉት ጥረት አጋሮች፣ ሀሳቦች እና ድጋፍ ፍለጋ የተሰባሰቡ ናቸው።
የ2024ቱ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ፌስቲቫል 20,000 ተሳታፊዎችን ያሰባሰበ ሲሆን በግዜው ተዘጋጅተው ከነበሩ ሁሉ ከፍተኛ ቁጥር ውክልና ከነበራቸው የወጣቶች ዝግጅቶች መካከል አንዱ ሆኖ አልፏል። የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ፌስቲቫል ከ191 ሀገራት የተውጣጡ 10,000 ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ከመስከረም 2 እስከ 7 በየካተሪንበርግ እየተካሄደ ይገኛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
© telegram sputnik_ethiopia
© telegram sputnik_ethiopia