በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የተከሰተው የኤቦላ ወረርሺኝ ስርጭት የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ እንደሆነ ባለሙያዎች ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የተከሰተው የኤቦላ ወረርሺኝ ስርጭት የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ እንደሆነ ባለሙያዎች ተናገሩ
ቀን ከቀን በወረርሺኙ የሚያዙ እና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ እንደሆነ የበሽታው ስርጭት መረጃዎች እንደሚጠቁሙ በኪንሻሳ ከተካሄደ ግምገማ በኋላ የቫይረስ ተመራማሪው ፕላሲድ ምባላ እና የመንግሥት ቃል አቀባይ ፓትሪክ ሙያያ ገልጸዋል።
🟠 ዋና ዋና ቁጥሮች፦ በኢቱሪ ግዛት ማዕከሉን አድርጎ ከግንቦት 7 ጀምሮ የተቀሰቀሰው ይህ የበሽታ ስርጭት፤ 6 ሺህ 843 በበሽታው የተያዙ እና 3 ሺህ 310 የሞቱ ሰዎችን የተመዘገቡበት ይህም ከአፍሪካ ሁለተኛው እጅግ ገዳይ ወረርሺኝ ያደርገዋል።
🟠 ክትባት፦ የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ከ70 ሺህ በላይ ክትባት ተረክቦ ክትባት መስጠት ጀምሯል። ባለሙያዎች እስካሁን የተፈቀደ ክትባት ለሌለው ለቡንዲቡግዮ ዝርያ የክትባቱን ውጤታማነት ያጠናሉ።
🟠 ቀጣናዊ ሁኔታ፦ ኡጋንዳ በኤቦላ ስርጭት ላይ ያወጀችውን የአደጋ ጊዜ ሐምሌ 21 ያነሳች ሲሆን የዓለም ጤና ድርጅትም ነሐሴ 18 ባወጣው መረጃ ሁኔታውን አረጋግጧል። ባለሙያዎች በተጠንቀቅ ላይ ሆነው እየቀነሰ የመጣውን የስርጭት አዝማሚያ ተከታትሎ ለማረጋገጥ ዝግጅት አድርገዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X