የኢትዮጵያ የብሪክስ ጉባኤ ተሳትፎ የደቡባዊውን ዓለም የጋራ ድምጽ ለማጠናከር ይረዳል - ናሬንድራ ሞዲ
09:18 12.09.2026 (የተሻሻለ: 09:49 12.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የብሪክስ ጉባኤ ተሳትፎ የደቡባዊውን ዓለም የጋራ ድምጽ ለማጠናከር ይረዳል - ናሬንድራ ሞዲ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ከህንድ አቻቸው ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡
ውይይቱ የኢትዮጵያ እና ህንድን የሁለትዮሽ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር ላይ ያለመ ነበር።
የውይይቱ ቁልፍ ውጤቶች፦
የኢኮኖሚ ትብብር፣ የመከላከያና የፀጥታ አጋርነት እንዲሁም የአቅም ግንባታን ጨምሮ በዋና ዋና ዘርፎች የታዩትን ዕድገቶች ገምግመዋል።
ሁለቱ መሪዎች በጋራ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል። በባለብዙ ወገን መድረኮችም በቅርበት ለመሥራት ቁርጠኝነታቸውን በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ የኢትዮጵያ በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ መገኘት የደቡባዊውን ዓለም የጋራ ድምጽ ለማጠናከር እንደረዳ አመልክተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ከህንድ አቻቸው ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡
ውይይቱ የኢትዮጵያ እና ህንድን የሁለትዮሽ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር ላይ ያለመ ነበር።
የውይይቱ ቁልፍ ውጤቶች፦
የኢኮኖሚ ትብብር፣ የመከላከያና የፀጥታ አጋርነት እንዲሁም የአቅም ግንባታን ጨምሮ በዋና ዋና ዘርፎች የታዩትን ዕድገቶች ገምግመዋል።
ሁለቱ መሪዎች በጋራ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል። በባለብዙ ወገን መድረኮችም በቅርበት ለመሥራት ቁርጠኝነታቸውን በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ የኢትዮጵያ በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ መገኘት የደቡባዊውን ዓለም የጋራ ድምጽ ለማጠናከር እንደረዳ አመልክተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X