የአውሮፓ ቀውስ ምዕራባውያን ግሎባሊስቶች የፈጠሩት ሥርዓታዊ ስህተት ውጤት ነው — ፑቲን

ሰብስክራይብ

የአውሮፓ ቀውስ ምዕራባውያን ግሎባሊስቶች የፈጠሩት ሥርዓታዊ ስህተት ውጤት ነው — ፑቲን

​"በአሁኑ ጊዜ በአጠቃላይ በአውሮፓ ውስጥ እየተከሰተ ያለው ነገር ሁሉ፤ 'ምዕራባውያን' ተብዬዎች አሊያም ይበልጥ በትክክል ለመግለጽ ምዕራባውያን ግሎባሊስቶች በፖለቲካ፣ በደህንነት እና በኢኮኖሚ ዘርፎች የፈጠሯቸው ሥርዓታዊ ስህተቶች ውጤት ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ገልጸዋል።

​ከቀዝቃዛው ጦርነት እና ከሶቪየት ኅብረት መፍረስ በኋላ የምዕራባውያን ግሎባሊስቶች "ሁሉም ነገር የተፈቀደ ነው" ብለው በማመን እንዲሁም ስህተት ሊሠሩ እንደማይችሉ በማሰብ ጥፋታቸው "እንደ በረዶ ኳስ" እየተንከባለለ እንዲከማች ፈቅደዋል ብለዋል።

​ምዕራባውያን መጀመሪያ በካውካሰስ ክልል ውስጥ ባሉ አሸባሪዎች እና ተገንጣዮች አማካኝነት በሩሲያ ላይ ጫና ለመፍጠር ሞክረው እንደነበርና፤ አሁን ደግሞ በዩክሬኑ የኒዮ-ናዚ ሥርዓት በኩል ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸሙ መሆናቸውን በደህንነት ዙሪያ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0