- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል። አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ይህ ፕሮግራምም ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት እና በአፍሪካ ሴቶች ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ

የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት እና በአፍሪካ ሴቶች ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ
ሰብስክራይብ
የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት የነዳጅ እና የምግብ ዋጋን በማናርና የሐዋላ ፍሰትን በማስተጓጎልና የዓለም አቀፍ አቅርቦት መዛባቱ ኢኮኖሚያዊ ጫና በግንባር ቀደምትነት የአፍሪካ ሴቶች እንዲሸከሙ እያስገደደ ነው።

የምግብ እና የነዳጅ ዋጋ ሲወደድ እንዲሁም ገቢ ሲቀንስ፣ የቤት ውስጥና የማህበረሰብን ኢኮኖሚያዊ ጫና ተሸክመው የሚያሳልፉት ሴቶች ናቸው። በመሆኑም ሀብታም አህጉር ይዘን ራሳችንን ከውጭ ተፅዕኖዎች እንዴት መጠበቅ እንደምንችል ትልቅ ትኩረት ሰጥተን ማሰብ አለብን” — ፋዴኬሚ አኬንፌዳሪን፣ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት።

በዛሬው የድራም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን በሩቅ የሚከሰቱ ግጭቶች ከዳካር እስከ ናይሮቢ የቤተሰብ ወጪንና የገበያ እንቅስቃሴን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነ ከታዋቂ የመብት ተሟጋች ጋር ዳስሰናል። የዓለም አቀፍ አደጋዎችን አህጉራዊ ተፅዕኖና የሴቶችን የኢኮኖሚ ጫና በጥልቀት የምንመረምርበትን ዝግጅት እንድትከታተሉ እንጋብዛለን። ለዚህም ናይጄሪያዊቷን የመብት ተሟጋች ፋዴኬሚ አኬንፌዳሪን አነጋግረናል።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezerAfripods SpotifyPocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0