"ያለ ሩሲያ እና አልጄሪያ እገዛ"ጠላቶቻችን በነሐሴ ወር መጨረሻ በኒያሜ ያካሄዱትን ጥቃት ያሸንፉ ነበር - ኒጀራዊ የፖለቲካ ባለሙያ
12:21 10.09.2026 (የተሻሻለ: 12:24 10.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
"ያለ ሩሲያ እና አልጄሪያ እገዛ"ጠላቶቻችን በነሐሴ ወር መጨረሻ በኒያሜ ያካሄዱትን ጥቃት ያሸንፉ ነበር - ኒጀራዊ የፖለቲካ ባለሙያ
“ለእነዚህ ሁለት ወንድም ሀገራት ታላቅ ምሥጋና አለን” ሲሉ ሱማይላ ካንጋይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የተጠናከረውን የኒያሜ እና ሞስኮ አጋርነት "መልካም" ሲሉ የገለጹት ባለሙያው፤ ከሩሲያ ጋር ያለው ወታደራዊ ግንኙነት "በሁሉም ዘርፍ" ይበልጥ እንደሚጠናከር እምነታቸውን ገልጸዋል።
የኒጀር ፕሬዚዳንት አብዱራሃማኔ ቺያኒ “ለሩሲያ የአፍሪካ ኮር አባላት ሙያዊ ብቃት” ለሩሲያ አምባሳደር ምሥጋናቸውን እንደገለጹ የሩሲያ ዲፕሎማሲያዊ ልዑክ ቀደም ሲል አስታውቋል።
ቪክቶር ቮሮፓዬቭ ከነሐሴ 22 እስከ 23 ምሽት የተሞከረውን የአመፅ ሙከራ ተከትሎ፤ በሀገሪቱ መሪ አቀባበል የተደረገላቸው የመጀመሪያው የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ልዑክ ኃላፊ ነበሩ።
የሱማሊያ ካንጋኢን ዝርዝር ትንተና በቪዲዮው ይመልከቱ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X