ኤፍ.ኤስ.ቢ ዩክሬን በሞስኮ የሚገኙትን የብሪታንያ አምባሳደር ለመግደል የጠነሰሰችውን ሴራ አከሸፈ

ሰብስክራይብ

ኤፍ.ኤስ.ቢ ዩክሬን በሞስኮ የሚገኙትን የብሪታንያ አምባሳደር ለመግደል የጠነሰሰችውን ሴራ አከሸፈ

የሩሲያ ፌዴራል የደህንነት አገልግሎት፤ በሞስኮ የብሪታንያ አምባሳደር እና ዲፕሎማቶች ላይ ጥቃት ለማድረስ መረጃ እንዲሰበስብ በዩክሬን የደህንነት አገልግሎት ተመልምሏል የተባለውን እና በብሪታንያ ኤምባሲ የጥበቃ ሠራተኛ የሆነውን የሩሲያ ዜጋ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።

ዋና ዋና ዝርዝሮች፦

ዩክሬን የምልምሉን መረጃ በመጠቀም በብሪታንያ አምባሳደር እና በኤምባሲው ሠራተኞች ላይ ጥቃት ለማድረስ አቅዳ ነበር፣

ግቡ ለንደን እና ሞስኮን ቀጥተኛ ግጭት ውስጥ ማስገባት እና ተጨማሪ የጦር መሣሪያዎችን ማግኘት ነበር፣

በቁጥጥር ስር የዋለው ምልምል የደህንነት መረጃዎችን ይሰበስብ የነበረው በዩክሬናዊው ጦማሪ ካርፔንኮ ትዕዛዝ ነበር፣

ዩክሬን የራሷን ስትራቴጂካዊ አጋሮች ጭምር የሽብር ድርጊቶች ዒላማ ለማድረግ ፈቃደኛ ነች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0