69% የሚሆኑ ኬንያውያን በአሜሪካ በጀት ሊገነባ የታቀደውን የኢቦላ ማዕከል ይቃወማሉ - የሕዝብ አስተያየት
20:18 09.09.2026 (የተሻሻለ: 20:24 09.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
69% የሚሆኑ ኬንያውያን በአሜሪካ በጀት ሊገነባ የታቀደውን የኢቦላ ማዕከል ይቃወማሉ - የሕዝብ አስተያየት
28% ምላሽ ሰጪዎች በላኢኪፒያ የአየር ኃይል ሠፈር ሊካሄድ የታሰበው ፕሮጀክት በዋናነት የአሜሪካን ጥቅም ለማስጠበቅ እና የውጭ ሀገር ታካሚዎችን ለማከም ያለመ ነው ሲሉ፤ 17% የሚሆኑት ደግሞ ተቃውሟቸውን ከሙስና ስጋት እና ግልጽ ካልሆኑ ስምምነቶች ጋር እንደሚያያዙት የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን የቲ.አይ.ኤፍ.ኤ ምርምር ተቋም የሕዝብ አስተያየት መስጫን ጠቅሰው ዘግበዋል።
የሕዝብ አስተያየቱ ከሰኔ 6 እስከ 15 በዘጠኝ ክልሎች በሚገኙ 2,048 ኬንያውያን የተሰጠ እና የስህተት ምጣኔው 2.18% እንደሆነ ተነግሯል።
ሰኔ 1 በዕቅዱ ዙሪያ በናኙኪ በተቀሰቀሱ ተቃውሞዎች፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች እና ወጣቶች አደባባይ ወጥተው ፕሮጀክቱ እንዲሰረዝ ጠይቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X