ሦስት አፍሪካውያን እግር ኳስ ተጫዋቾች ለ2026ቱ የባሎንዶር ምርጥ ግብ ጠባቂ ሽልማት ታጩ
12:44 09.09.2026 (የተሻሻለ: 12:54 09.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሦስት አፍሪካውያን እግር ኳስ ተጫዋቾች ለ2026ቱ የባሎንዶር ምርጥ ግብ ጠባቂ ሽልማት ታጩ
ቮዚንሃ (ኬፕ ቨርዴ፣ ኮሎ-ኮሎ)፣
ያሲን ቡኑ (ሞሮኮ፣ አል ሂላል)፣
ኤድዋርድ ሜንዲ (ሴኔጋል፣ አል አህሊ)።
በ10 ዕጩዎች ዝርዝር ውስጥ በፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ የሚጫወተው ሩሲያዊው ግብ ጠባቂ ማትቬይ ሳፎኖቭ ይገኝበታል።
አሸናፊው ጥቅምት 16 በለንደን በሚካሄደው ሥነ-ሥርዓት ይፋ ይሆናል።
ይህ የግብ ጠባቂዎች ሽልማት የባሎንዶር ሽልማትን በማሸነፍ ብቸኛው ግብ ጠባቂ የነበረው እና የምንግዜም ምርጡ ግብ ጠባቂ ተብሎ በሚጠራው የሶቪየት ኅብረት እግር ኳስ ተጫዋች ሌቭ ያሺን ስም የተሰየመ ነው።
ምሥል ከግራ ወደቀኝ፦ ኤድዋርድ ሜንዲ፣ ቮዚንሃ፣ ያሲን ቦኖ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X