የደቡብ አፍሪካ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት በኔልሰን ማዴላ ቅርሶች ዕጣ ፈንታ ዙሪያ ውሳኔ ሊሰጥ ነው - መገናኛ ብዙኃን
11:38 09.09.2026 (የተሻሻለ: 11:44 09.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት በኔልሰን ማዴላ ቅርሶች ዕጣ ፈንታ ዙሪያ ውሳኔ ሊሰጥ ነው - መገናኛ ብዙኃን
የደቡብ አፍሪካ የቅርሶች ኤጀንሲ እና የባሕል ሚኒስቴር 29 የኔልሰን ማዴላ ታሪካዊ መታሰቢያዎች የሀገሪቱ ብሔራዊ ቅርሶች በመሆናቸው ያለ ሕጋዊ ፈቃድ ወደ ውጭ ሀገር ሊወጡ አይገባም ሲሉ እየተከራከሩ ነው።
የማንዴላ መታወቂያ ካርድ እና ታዋቂ ሸሚዞቻቸውን የሚያካተቱት እነዚህ ቅርሶች፤ በማንዴላ የመጀመሪያ ልጅ ማካዚዌ ፈቃድ አሜሪካ በሚገኝ የጨረታ ድርጅት በኩል ለጨረታ ቀርበዋል። ማካዚዌ በአባቷ የትውልድ መንደር ኩኑ ከመካነ-መቃብራቸው አጠገብ ለሚገነባ የመታሰቢያ ፓርክ ፕሮጀክት ገንዘብ ለማሰባሰብ ጨረታውን እንደፈቀደች ገልጻለች።
ጨረታው ለመጀመሪያ ጊዜ እ.አ.አ በ2021 ይፋ የተደረገ ቢሆንም፤ የደቡብ አፍሪካ የቅርሶች ኤጀንሲ ያቀረበውን ሕጋዊ ጥያቄ ተከተሎ በ2022 በፍርድ ቤት እንዲታገድ ተደርጓል። የደቡብ አፍሪካ ፍርድ ቤቶች ጨረታው እንዲቀጥል ቢፈቅዱም፤ መንግሥት ሽያጩን ለማስቆም የሚያደርገውን ሕጋዊ ጥረት በመቀጠሉ ጨረታው ዳግም እንዲቆም ተደርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/2
© telegram sputnik_ethiopia

2/2
© telegram sputnik_ethiopia
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
2/2
© telegram sputnik_ethiopia