የሮስቴክ 'ሲታደል' የአየር መከላከያ ሥርዓት ለመጀመሪያ ጊዜ በውጭ ሀገር ዓለም አቀፍ ትርዒቱን ሊያቀርብ ነው

© telegram sputnik_ethiopiaየሮስቴክ 'ሲታደል' የአየር መከላከያ ሥርዓት ለመጀመሪያ ጊዜ በውጭ ሀገር ዓለም አቀፍ ትርዒቱን ሊያቀርብ ነው
የሮስቴክ 'ሲታደል' የአየር መከላከያ ሥርዓት ለመጀመሪያ ጊዜ በውጭ ሀገር ዓለም አቀፍ ትርዒቱን ሊያቀርብ ነው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.09.2026
ሰብስክራይብ

የሮስቴክ 'ሲታደል' የአየር መከላከያ ሥርዓት ለመጀመሪያ ጊዜ በውጭ ሀገር ዓለም አቀፍ ትርዒቱን ሊያቀርብ ነው

ይህ እጅግ ዘመናዊ ሥርዓት በግብፅ በሚካሄደው 'ኤል አላሜይን የ 2026 ዓለም አቀፍ የአየር ትርዒት' የጦር መሳሪያዎች ኤግዚቢሽን ላይ ዓለም አቀፍ የመጀመሪያ ትርዒቱን እንደሚያቀርብ ሮስቴክ አስታውቋል።

ቋሚ ተቋማትን እና ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ከድሮን ስጋቶች ከፍተኛ ደረጃ ባለው መልኩ ለመጠበቅ የተነደፈው 'ሲታደል'፣ ባለ 30 ሚሊሜትር አውቶማቲክ መድፎች የታጠቀ ሲሆን በማንኛውም የአየር ሁኔታ ውስጥ በሙሉ አቅሙ 24 ሠዓት ሙሉ የመስራት ብቃት አለው።

ይህ የአየር መከላከያ ኮምፕሌክስ ዒላማዎችን ከመለየት ጀምሮ እስከ መደምሰስ ድረስ በከፍተኛ ሁኔታ በራስ-ሰር የሚሰራ ሲሆን፣ በተወሰነ የጉዞ መስመር ነጥብ ላይ እንዲፈነዳ ፕሮግራም የሚደረግ ዘመናዊ ጥይት የተገጠመለት ነው።

"ሥርዓቱ የቁልፍ ተቋማትን የቅርብ እርቀት ቀጣናዎች በአስተማማኝ ሁኔታ መሸፈን የሚችል ሲሆን፣ ከሌሎች ፀረ-ድሮን መሳሪያዎች ጋር በመቀናጀት የተደራረበ የአየር መከላከያ አካል ሆኖ መስራት ይችላል" ሲል ሮስቴክ ይፋ አድርጓል።

የኤል አላሜይን ዓለም አቀፍ የአየር ትርዒት 2026 እ.አ.አ ከመስከረም 8 እስከ 10 2026 በግብፅ ኤል አላሜይን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እየተካሄደ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0