የሀገር ውስጥ ገንዘብ ቀውሶችን ለመፍታት የሚያስችሉ መፍትሄዎች እንዲበጁ ጥሪ ቀረበ

ሰብስክራይብ

የሀገር ውስጥ ገንዘብ ቀውሶችን ለመፍታት የሚያስችሉ መፍትሄዎች እንዲበጁ ጥሪ ቀረበ

በአፍሪካ የተደራዳሪዎች ቡድን የዛምቢያ ዋና ተደራዳሪ ዳቪድ ካሉባ 14ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረትና ልማት ጉባኤ የሀገር ውስጥ ገንዘብ (የምንዛሬ) ተጋላጭነቶች ሊፈቱ እንደሚገባ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ የምንዛሬ ተመን ስጋቶች በአፍሪካ የአየር ንብረት ኢንቨስትመንትን እያደናቀፉ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ካሉባ፤ ከፍተኛ የብድር ወለድ መጠን ለአየር ንብረት እና ለልማት ፕሮጀክቶች ፋይናንስ ለማግኘት ዋና ማዕቀብ ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል። ከ9 እስከ 10 በመቶ በሚደርስ ወለድ መበደር ለብዙ ፕሮጀክቶች እጅግ ውድ መሆኑን የጠቀሱት ተደራዳሪው፣ ከ5 እስከ 6 በመቶ አካባቢ የሚሆን የብድር ወለድ ግን ፋይናንስን የበለጠ ተመጣጣኝ ያደርገዋል ብለዋል።

ካሉባ በተጨማሪም ለአፍሪካ ኢኮኖሚዎች የተደቀነውን የምንዛሬ አለመጣጣም አጉልተው ያሳዩ ሲሆን፤ ኢንቨስተሮች ብድሩን በነጻ የምንዛሬ ዶላር ወስደው ገቢያቸውን ግን በሀገር ውስጥ ገንዘብ የሚሰበስቡ በመሆኑ ለምንዛሬ ኪሳራ ይጋለጣሉ ብለዋል።

እነዚህን ስጋቶች ለመቀነስ እና በመላው አፍሪካ ለኢንቨስትመንት የበለጠ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር በሀገር ውስጥ ገንዘብ ብድር እና ፋይናንስ የመስጠት አሰራር እንዲዘረጋ ጥሪ አቅርበዋል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0