- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል። አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ይህ ፕሮግራምም ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

ከቃል ኪዳን ወደ ትግበራ ኃይል፡ የአፍሪካ የአየር ንብረት አጀንዳ

ከቃል ኪዳን ወደ ትግበራ ኃይል፡ የአፍሪካ የአየር ንብረት አጀንዳ
ሰብስክራይብ
አፍሪካ ለካርቦን ልቀት 4 በመቶ እንኳ ሳታበረክት፣ ከሚያስፈልጋት 277 ቢሊዮን ዶላር በጀት ያገኘችው 11 በመቶውን ብቻ ነው። ይህ ፕሮግራም ከአየር ንብረት በደል ወደ አፍሪካ መሪነት የሚደረገውን ጉዞ ይዳስሳል።

ከማይተገበሩ ቃል ኪዳኖች ወደ ተግባራዊ አፈጻጸም መሸጋገር አለብን። በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው ኮፕ 32 ይህ ተግባራዊ ይሆናል የሚል እምነት አለን። የኢትዮጵያ መንግስት ቅድመ ዝግጅቱን ከሚጠበቀው በላይ በፍጥነት እያከናወነ ሲሆን፣ የመሪነት ሚናውም በዚህ ሂደት ከፍተኛ ትኩረት ያገኛል" ሲሉ ዶ/ር ዮሴፍ አመሓ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን ከባድ ድርቅና ጎርፍ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ ከመፈተኑ ጀምሮ፣ እስከ ታላላቅ የድርድር መድረኮች ቃላት ከድርጊት የሚበልጡበትን አዝማሚያ ጨምሮ፣ አፍሪካ የአየር ንብረት ሉአላዊነቷን ለማስከበር የምታደርገውን የረጅም ጊዜ ትግል ታላቅ ታሪክ አካል አድርገን እናቀርበዋለን። ዝግጅቱን ከ 14ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥና ልማት ጉባኤ አንጻር የምናቀርበው ሲሆን፣ በጉባኤ ላይ ተገኝተን ዮሴፍ አመሓን (ዶ/ር)፣ በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን የአየር ንብረት ተማራማሪ ጨምሮ የተለያዩ ተሳታፊዎችን አውርተናል።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezerAfripods SpotifyPocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0