ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በ15ኛው ዓመታዊ የኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ዱባይ ገቡ
12:15 07.09.2026 (የተሻሻለ: 12:24 07.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በ15ኛው ዓመታዊ የኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ዱባይ ገቡ
ፕሬዝዳንቱ፣ ከጳጉሜን 2 እስከ 4 2018 በዱባይ ዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል ለሚካሄደው ዓመታዊ የኢንቨስትመንት ጉባኤ ከፍተኛ የሀገር ውስጥ የልዑካን ቡድን በመመራት ወደ ስፍራው አቅንተዋል።
ዋና ዋና መረጃዎች፦
🟠 ጉባኤው "ዓለም አቀፍ ብልጽግናን እንደገና መቅረጽ፦ ለአካታችና ዘላቂ ወደፊት አዳዲስ የኢንቨስትመንት አማራጮችን መክፈት" በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል።
🟠 የዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ዘላቂ ልማት፣ ኢኖቬሽን እና ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት አጋርነቶች ላይ ያተኩራል።
🟠 ኢትዮጵያ የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብና የሀገር ውስጥ ኢኮኖሚ ሪፎርሟን ለማስተዋወቅ ትልቅ መድረክ ይሆንላታል ተብሏል።
🟠 የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዓለም አቀፍ ባለሀብቶች፣ የንግድ ሥራ አስፈፃሚዎችና ተመራማሪዎች በጉባኤው ይሳተፋሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X