ቻይና ማርስን በመመርመር ረገድ ናሳን ልትቀድም ነው
08:55 07.09.2026 (የተሻሻለ: 09:04 07.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቻይና ማርስን በመመርመር ረገድ ናሳን ልትቀድም ነው
ቻይና ቲያንዌን-3 የተሰኘውን ታላቅ የሮቦቲክ ህዋ ተልዕኮ በ2028 ለማስወንጨፍ ያቀደች ሲሆን፤ ተልዕኮው በ2031 ወደ 500 ግራም የሚመዝን የማርስ የናሙና አካላትን ይዞ ወደ ምድር ይመለሳል ተብሎ ይጠበቃል።
"በሚመለሱት ናሙናዎች ላይ በሚደረገው ዝርዝር ምርመራ፣ ሳይንቲስቶች ተአማኒነት ያላቸው የሕይወት ምልክቶችን ለማግኘት ተስፋ ያደርጋሉ" ሲሉ የቻይና የሳይንስ አካዳሚ ባለሙያ ሆው ዜንግቺያን ገልጸዋል።
ናሳ በ'ፐርሰቪያራንስ' ተልዕኮው ናሙናዎችን የሰበሰበ ቢሆንም፣ አሜሪካ በቂ የፋይናንስ በጀት በማጣቷ ምክንያት ተልዕኮው ባልተጠበቀ ዕንቅፋት ውስጥ ወድቋል።
"የማርስ ናሙና መመለሻ ፕሮጀክት መሰረዝ፤ ከማርስ ናሙናዎችን ይዞ መመለስ ለአሜሪካ እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ከመቀበል ውጪ ሌላ ትርጉም ሊኖረው አይችልም" ሲሉ የህዋ ሳይንቲስቷ ቪክቶሪያ ሃሚልተን አምነዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X