የአሜሪካ መልዕክተኞች ከሞስኮ እና ኪዬቭ ውይይቶች በኋላ አዎንታዊ ምላሽ ሰጡ
የአሜሪካ መልዕክተኞች ከሞስኮ እና ኪዬቭ ውይይቶች በኋላ አዎንታዊ ምላሽ ሰጡ
የፕሬዝዳንቱ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከፑቲን እና ከዘለንስኪ ጋር ከተገናኙ በኋላ፣ በሞስኮ እና በኪዬቭ በተካሄዱት ውይይቶች ውጤት መርካታቸውን ተናግረዋል። በሌላ በኩል ጃሬድ ኩሽነር ዋሺንግተን በ"ሰላም የውል ረቂቅ” ላይ እየሠራች መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 ዊትኮፍ ስለ ውይይቶቹ፦ በሞስኮ እና በኪዬቭ ከተካሄዱት የሰላም ውይይቶች ውጤት በኋላ "ጥሩ ስሜት ይሰማናል" ሲሉ ዊትኮፍ በኪዬቭ ለጋዜጠኞች የተናገሩ ሲሆን፤ አሜሪካ ለግጭቱ ወታደራዊ ሳይሆን ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ እንደምትፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።
🟠 የትራምፕ ግፊት፦ ይህን የዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮ ራሳቸው ትራምፕ በግል መጠየቃቸውን የጠቆሙት ዊትኮፍ፣ በሞስኮ እና በኪዬቭ መካከል ውይይት እንደገና ማስጀመር ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት በጣም አስፈላጊ ነው ብለዋል።
🟠 ከኡሽነር ስለውይይት ቅርጽ፦ ኩሽነር፣ ድርድሩ ሩሲያ፣ ዩክሬን እና አሜሪካን ወደሚያሳትፍ የሦስትዮሽ የውይይት ቅርጽ እንደሚመለስ ተስፋቸውን አንጸባርቀዋል።
🟠 የፑቲን አቋም፦ የክሬምሊን አማካሪ ዩሪ ሻኮቭ እንደገለጹት፣ ቅዳሜ ዕለት በሞስኮ በተካሄደው ስብሰባ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ለዩክሬን ግጭት "መንስኤ የሆኑትን መነሻ ምክንያቶች በሙሉ" መፍትሔ መስጠት እንደሚያስፈልግ አስረግጠዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X