ሰብአዊ እርዳታ በአፍሪካ፦ የጥገኝነት አስተሳሰብን እና ልማድን እንዴት ማስወገድ ይቻላል ? - ቡሩንዲያዊቷ ባለሙያ ያብራራሉ
12:45 06.09.2026 (የተሻሻለ: 12:54 06.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሰብአዊ እርዳታ በአፍሪካ፦ የጥገኝነት አስተሳሰብን እና ልማድን እንዴት ማስወገድ ይቻላል ? - ቡሩንዲያዊቷ ባለሙያ ያብራራሉ
የረጅም ጊዜ ድጋፎች ተቀባይ ብቻ ከሚያደርግ ቁሳቁስ ስርጭት ይልቅ አቅምን መገንባት ላይ ቅድሚያ መስጠት አለባቸው ሲሉ ኤውላሪ ኢራኮዜ በየዓመቱ መስከረም 5 (ነሐሴ 30) የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የበጎ አድራጎት ቀን በማስመልከት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
እሳቸው፣ ለቀውስ ምላሽ ለመስጠት አሳማኝ ከሆነው የድንገተኛ ጊዜ እርዳታ እና ልማታዊ እርዳታ መካከል ያለውን ልዩነት በግልጽ መለየት ወሳኝ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው እአስገንዝበዋል።
በዚህም ምክንያት፣ ኢራኮዜ በቀጥታ በሚሰጡ ተራ እርዳታዎች እና እድገቶች ላይ ከመደገፍ ይልቅ እንደ አነስተኛ ብድር፣ የሕብረት ሥራ ማኅበራትን መደገፍ፣ የሙያ ሥልጠና እና ለሀገር ውስጥ ስራ ፈጣሪዎች ሙያዊ መሪነት መስጠትን የመሳሰሉ መሳሪያዎችን ማስቀደም እንደሚገባ ሞግተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X