ቻይናውያን ሳይንቲስቶች ከባሕር ውኃ ዩራኒየምን ከአሜሪካው መስፈርት በ8 እጥፍ በፍጥነት የሚያወጣ አዲስ ግኝት ይፋ አደረጉ

ሰብስክራይብ

ቻይናውያን ሳይንቲስቶች ከባሕር ውኃ ዩራኒየምን ከአሜሪካው መስፈርት በ8 እጥፍ በፍጥነት የሚያወጣ አዲስ ግኝት ይፋ አደረጉ

በኪንግዳኦ በሚገኘው የቻይና የሳይንስ አካዳሚ የተሠራው «ፎስኬጅ» የተሰኘ ስፖንጅ መሰል ሞለኪውላዊ ቁሳቁስ፣ በባሕር ውኃ ውስጥ የሚገኘውን የሟሟ ዩራኒየም ለማጥመድ የፎስፌት ስብስብን ይጠቀማል።

◼ ከተፈጥሮ የባሕር ውኃ ጋር በተደረገ ሙከራ፣ በአንድ ግራም ቁሳቁስ እስከ 50.4 ሚሊግራም ዩራኒየም ማውጣት የተቻለ ሲሆን፤ የአሜሪካ የኃይል መምሪያ መለኪያ መስፈርት ግን 6 ሚሊግራም በግራም ነው።

◼ ተመራማሪዎቹ ቁሳቁሱን ደግመው ጥቅም ላይ ሊውሉ ወደሚችሉ ጥቃቅን የነጥብ እንክብሎች የለወጡት ሲሆን፣ በዚህም በአንድ ግራም 22.55 ሚሊግራም ዩራኒየም ማውጣት ተችሏል።

◼ ቁሳቁሱ በተለይም ከባሕር ውኃ ዩራኒየምን ማውጣትን አስቸጋሪ የሚያደርገው «ቫናዲየም» የተሰኘው ንጥረ ነገር ባለበት ሁኔታም ቢሆን፣ ዩራኒየምን ብቻ ለይቶ የመሳብ ከፍተኛ አቅም አሳይቷል።

ቴክኖሎጂው በኢኮኖሚያዊ መልኩ በስፋት ጥቅም ላይ መዋል ከተቻለ፣ ውቅያኖሶች ግዙፍ የኒውክሌር ነዳጅ ማከማቻ በመሆን፤ የባሕር ውኃ በምድር ላይ ካሉ እጅግ ስትራቴጂካዊ ሀብቶች አንዱ ሊሆን ይችላል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0