- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል። አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ይህ ፕሮግራምም ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

ኤል ኒኞ 2026፦ የአፍሪካ የጽናት ፈተና ከድርቅ እስከ ጎርፍ

ኤል ኒኞ 2026፡ የአፍሪካ የጽናት ፈተና፣ ከድርቅ እስከ ጎርፍ
ሰብስክራይብ

“አፍሪካ በከፍተኛ ደረጃ ስንዴ የምታስገባ አህጉር ናት። አፍሪካ በየዓመቱ ከ50 ሚሊዮን ቶን በላይ ስንዴ ታስገባለች። ለዚህም ከ20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ታወጣለች። ስለዚህ ኤል ኒኞ በሚከሰትበት ጊዜ የስንዴ ምርት መቀነስ፣ የሌሎች እህሎች ምርት መቀነስ ነው... ይህም የገበያ ተጋላጭነትንና የንግድ ሚዛን መዛባቱን የበለጠ ያባብሰዋል” ሲሉ በሞሮኮ የዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ሳይንቲስት እና የመኸር ስንዴ እርባታ መሪ ተመራማሪው ታደሰ ዉለታው (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናገግረዋል።

በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን የ2026 ኤል ኒኞ በአፍሪካ ላይ የሚያሳድረውን ድርቅ፣ ሙቀትና የጎርፍ ስጋት እንዲሁም በግብርና፣ በገበያና በምግብ ዋስትና ላይ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ይዳስሳል። የችግሩ መፍትሔም የቀደመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ መስጠት ተጽእኖውን ለመቋቋም ምን ጥቅም አላቸው የሚለውን ጉዳይና ተያያዥ ነጥቦችን በተመለከተ በሞሮኮ ራባት የሚገኘው የድርቅ አከባቢዎች ዓለም አቀፍ የግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ሳይንቲስት እና የመኸር ስንዴ እርባታ መሪ ተመራማሪው ታደሰ ዉለታው (ዶ/ር) አነጋግረናቸዋል

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0