ኢትዮጵያ ማሽላን የኢንቨስትመንትና የግብርና ትራንስፎርሜሽን ማዕከል አድርጋ በአፍሪካ የምግብ ሥርዓት ፎረም አቀረበች

© SHAFFY RWAKAኢትዮጵያ ማሽላን የኢንቨስትመንትና የግብር
ኢትዮጵያ ማሽላን የኢንቨስትመንትና የግብር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.09.2026
ሰብስክራይብ
በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው የአፍሪካ የምግብ ሥርዓት ፎረም ኢትዮጵያ ማሽላን ከተለመደ የምግብ ሰብልነት ባሻገር ለስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት፣ ለእሴት ጭማሪ፣ ለምግብ ዋስትና እና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚሆን የኢኮኖሚ ማዕከል አድርጋ አስተዋውቃለች።
🌍 የኢትዮጵያን የማሽላ ዘርፍ አቅም ከካፒታል፣ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ ከግሉ ዘርፍ እና ከውጭ ገበያዎች ጋር የሚያስተሳስር ውይይት ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ቁልፍ ተሞክሮ፦
🟠 የግሉ ዘርፍ በዘርፉ በስፋት እንዲሰማራ የተሻሻሉ ሕጎች፣ የኮንትራት እርሻ አዋጅ፣ የግብር ማበረታቻዎች እና የአግሮ-ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተመቻችተዋል።
🟠 የማሽላ ምርት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈን አልፎ በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና በኮሜሳ በኩል ለውጭ ገበያ የሚቀርብበት አሰራር ተዘርግቷል።
🤝 በዚህም የኢትዮጵያን ተሞክሮ መሰረት በማድረግ ማሽላን ለአኅጉራዊ የግብርና እድገት ለመጠቀም የሚያስችል 'የፓን አፍሪካ የማሽላ ጥምረት' ተመስርቷል።
አዳዲስ ዜናዎች
0