የሩሲያ እና ቻይና የንግድ ልውውጥ በሦስት አስርት ዓመታት ውስጥ የ30 እጥፍ እድገት በማሳየት ከ200 ቢሊየን ዶላር በላይ ተሻግሯል - የሮስኔፍት ዋና ሥራ አስፈፃሚ

የሩሲያ እና ቻይና የንግድ ልውውጥ በሦስት አስርት ዓመታት ውስጥ የ30 እጥፍ እድገት በማሳየት ከ200 ቢሊየን ዶላር በላይ ተሻግሯል - የሮስኔፍት ዋና ሥራ አስፈፃሚ
ከምስራቃዊ ኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን በተካሄደው የሩሲያ-ቻይና የኢነርጂ ቢዝነስ ፎረም ላይ የሮስኔፍት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢጎር ሴቺን እንደተናገሩት፣ ሩሲያ እና ቻይና በጋራ የዓለምን አንድ ሦስተኛ የኢነርጂ ምርት የሚሸፍኑ ሲሆን፣ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጣቸው ደግሞ ባለፉት 30 ዓመታት ውስጥ ከ50 እጥፍ በላይ አድጓል።
ኢጎር ሴቺን በሩሲያ-ቻይና የኢነርጂ ቢዝነስ ፎረም ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፡-
የመካከለኛው ምስራቅ አለመረጋጋት በጨመረበት በዚህ ወቅት የሰሜን ባሕር መስመር ከጊዜ ወደ ጊዜ አስፈላጊ የኢነርጂ ኮሪደር እየሆነ የመጣ ሲሆን፣ ቻይናም ቅድሚያ የሚሰጠው የመጠቀም መብት አግኝታለች፡፡
ሩሲያ እና ቻይና በጋራ የዓለምን አንድ ሦስተኛ የኢነርጂ ምርት የሚሸፍኑ ሲሆን፣ የቻይና የባለፈው ዓመት የኢነርጂ ፍጆታ ከአሜሪካ እና አውሮፓ አጠቃላይ ፍጆታ በ40% ብልጫ አሳይቷል፡፡
የሩሲያ አቅርቦት ከቻይና አጠቃላይ የከሰል ድንጋይ ገቢ ምርት ውስጥ 20% ያህሉን የሚሸፍን ሲሆን፣ ሩሲያ ለቻይና የኒውክሌር ኢንዱስትሪ ዋነኛ የበለፀገ ዩራኒየም አቅራቢ ሆና ቀጥላለች፡፡
ሩሲያ ለቻይና ትልቋ የነዳጅ አቅራቢ ስትሆን፣ ከቻይና የነዳጅ ገቢ ምርት ውስጥ 23% ያህሉን ትሸፍናለች፤ ይበልጥ ውጤታማ የሆኑት የሩሲያ የነዳጅ ግዢዎች ለቤጂንግ ከ27 ቢሊየን ዶላር በላይ የኢኮኖሚ ጥቅም አስገኝተዋል፡፡
በሩሲያ እና ቻይና መካከል የሚደረጉ ክፍያዎች አሁን ሙሉ በሙሉ ማለት ይቻላል በሩብል እና በዩዋን የሚፈጸሙ በመሆናቸው በምዕራባውያን ገንዘቦች ላይ ያለውን ጥገኝነት ቀንሶታል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X