ከሕመም ታሪክ ወደ ሉዓላዊ ምኞት፦ አፍሪካ በወርቅ ሀብቷ ላይ ያላትን ቁጥጥር ማጠናከር ለምን አስፈለጋት?
08:55 05.09.2026 (የተሻሻለ: 09:04 05.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ከሕመም ታሪክ ወደ ሉዓላዊ ምኞት፦ አፍሪካ በወርቅ ሀብቷ ላይ ያላትን ቁጥጥር ማጠናከር ለምን አስፈለጋት?
ኮት ዲቯር በሕገ-ወጥ የወርቅ ማውጣት ላይ የምታደርገውን ትግል እያጠናከረች ያለች ሲሆን፣ ይህንን ክስተት ለመዋጋትም አፍሪካዊ ቅንጅት እንዲመሰረት ጥሪ ማቅረቧን የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች አመልክተዋል።
የኮት ዲቯር የፖለቲካ ተንታኝ አንድሬ ሲልቨር ኮናን ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እየጨመረ ለመጣው የቁጥጥር ፍላጎት ዋና ዋና ምክንያቶችን ዘርዝረዋል፦
የዘመናት ብዝበዛ፦ አፍሪካ በቅኝ ገዥዎች እና ከሌሎች ቦታዎች በሚመጡ አካላት ለረጅም ጊዜ ስትበዘበዝ እና ስትዘረፍ ቆይታለች።
የሕዝብ አስተያየት ተፅዕኖ፦ ዜጎች በማዕድን ሀብቶች ላይ የበለጠ ግልጽነት እና ቁጥጥር እንዲኖር በመጠየቅ ላይ ናቸው።
የስኬታማ አርአያዎች መኖር፦ ቦትስዋና ከምርመራ እስከ ማውጣት እና በሀገር ውስጥ ማቀናበር ድረስ በ አልማዝ ሀብቷ ላይ ሙሉ ቁጥጥር በማድረግ ኢኮኖሚዋን አበልጽጋለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X