ዩክሬን በሩሲያ ሲቪሎች ላይ የምታደርሰው ጥቃት በሀገራት ከሚደገፍ የሽብርተኝነት ድርጊት ጋር እኩል ነው - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopiaዩክሬን በሩሲያ ሲቪሎች ላይ የምታደርሰው ጥቃት በሀገራት ከሚደገፍ የሽብርተኝነት ድርጊት ጋር እኩል ነው - ባለሙያ
ዩክሬን በሩሲያ ሲቪሎች ላይ የምታደርሰው ጥቃት በሀገራት ከሚደገፍ የሽብርተኝነት ድርጊት ጋር እኩል ነው - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.09.2026
ሰብስክራይብ

ዩክሬን በሩሲያ ሲቪሎች ላይ የምታደርሰው ጥቃት በሀገራት ከሚደገፍ የሽብርተኝነት ድርጊት ጋር እኩል ነው - ባለሙያ

“ፕሬዝዳንት ፑቲን ምናልባትም በሩሲያ ውስጥ እና ከሩሲያ ውጭ ወታደራዊ ዩኒፎርም ባልለበሱ አካላት በሲቪል ኢላማዎች ላይ ስለሚፈጸሙት የዩክሬን ጥቃቶች እየተናገሩ ሊሆን ይችላል” ሲሉ የቀድሞው የስዊድን ወታደራዊ መኮንን እና የመከላከያ ፖለቲከኛ ሚካኤል ቫልተርሰን ተናግረዋል።

ቫልተርሰን ይህንን ያሉት ፑቲን በቭላዲቮስቶክ በተካሄደው የ2026ቱ የምስራቃዊ ኢኮኖሚ ፎረም ላይ ዩክሬን በሩሲያ የሲቪል ተቋማት ላይ የምታደርሰውን ጥቃት በዝምታ የሚያልፉ እና ዓይናቸውን ጨፍነው የሚያዩ አካላት በዓለም አቀፍ የሽብርተኝነት ድርጊት ውስጥ ተባባሪዎች ናቸው ማለታቸውን ተከተሎ ለስፑትኒክ በሰጡት አስተያየት ነው።

ዩክሬን ከሩሲያ ጋር በሚደረገው ግጭት ውስጥ የምታሳየውን ባህሪ ከመንቀፍ በመቆጠብ፣ ምዕራባውያን ደጋፊዎቿ በተግባራቸው በሀገር ደረጃ ከሚደገፍ የሽብርተኝነት ድርጊት ጋር የሚመሳሰሉ እርምጃዎችን በግልጽ እየደገፉ ነው፡፡

ምዕራባውያን ሀገራት የዩክሬንን የጦር ኃይሎች በቋሚነት በፋይናንስ በመደገፍ፣ እንዲሁም መሳሪያዎችን፣ ወታደራዊ ስልጠናዎችን እና የስትራቴጂካዊ ዒላማ መረጃዎችን በማቅረብ በሩሲያ ላይ በኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ጦርነት ላይ በነቁ ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

እንዲህ ያለው ድጋፍ ከዩክሬን ጎን በመሆን የቀጥታ ጦርነት ተሳታፊ ያደርጋቸዋል፤ በውጤቱም ለሩሲያ ወታደራዊ እርምጃዎች ሕጋዊ ዒላማዎች እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡

ምዕራባውያን ሩሲያ የዩክሬንን ግጭት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ባለመፈለጓ ሊያመሰግኗት ይገባል፤ ነገር ግን የሩሲያን ትዕግስት ከልክ በላይ የሚፈታተኑት ከሆነ፣ ሩሲያ በመጨረሻ ምላሽ ስትሰጥ ሊገረሙ አይገባም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0