በዘላቂ ሥነ-ምኅዳራዊ ግብርና ውጤታማ የሆኑ ወጣቶች ተሸለሙ

ሰብስክራይብ

በዘላቂ ሥነ-ምኅዳራዊ ግብርና ውጤታማ የሆኑ ወጣቶች ተሸለሙ

የኢትዮጵያ ዘላቂ ሥርዓተ-ምግብና ሥነ-ምኅዳራዊ ግብርና ሕብረት በዘላቂ ሥነ-ምኅዳራዊ ግብርና ዘርፍ ተሰማርተው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ወጣቶች እውቅና እና ሽልማት ሰጥቷል።

የሕብረቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ባዩሽ ጸጋዬ እንደገለጹት፣ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀው ይህ የእውቅና መርሃ-ግብር በዘርፉ በመሰማራት ዘላቂ የሥራ እድል የፈጠሩ፣ የራሳቸውንና የማኅበረሰቡን ኑሮ ማሻሻል የቻሉ ወጣቶችን ለማበረታታት ያለመ ነው።

ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም የእውቅና ሥነ-ስርዓቱ፡-

የወጣቶችን የግብርና ዘርፍ የፈጠራ ክህሎት ለማጎልበት፣

ዘላቂ የምግብ ሥርዓትና ሥነ-ምኅዳርን እውን ለማድረግ የሚደረጉ ሀገራዊ ጥረቶችን ለመደገፍ የጎላ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።

በእውቅና እና ሽልማት መርሃ-ግብሩ ላይ ለተመረጡት ወጣቶች የገንዘብ ሽልማት እና የምስክር ወረቀት እንደተበረከተላቸው የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግቧል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0