- Sputnik አፍሪካ, 1920
Continental Drift
በአፍሪካ ቅርፅ እየቀየሩ ያሉትን እንደዚሁም የደቡባዊውን ዓለም ክፍል ሚና በአዲስ መልክ እየገለጹ ያሉትን ስር ነቀል ለውጦች የሚቃኝ ፕሮግራም ነው። ትዕይንቱ ፖሊሲዎች፣ ገበያዎች እና ፈጠራዎች ከዕለት ተዕለት ሕይወት ጋር እንዴት እንደሚገናኙ በመመርመር በእውነታ ላይ የተመሰረቱ ግንዛቤዎችን እና ትክክለኛ የአፍሪካ አመለካከቶችን ያቀርባል።

አፍሪካ የፈጠራ ባለጸግነቷን እንዴት ትቆጣጠራለች?

አፍሪካ የፈጠራ ባለጸግነቷን እንዴት ትቆጣጠራለች?
ሰብስክራይብ

አፍሪካዊ ሙዚቃ እና የባህል ኢንዱስትሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ እያደጉ ቢመጡም፣ እውነተኛ ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራሳችንን ድምፅ እና የፈጠራ ሥራዎች ያለ የውጭ ማሻሻያ በራሳችን መንገድ መቅረጽና መቆጣጠር ወሳኝ ነው።

“መጀመሪያውና ትልቁ ነገር አፍሪካውያን የራሳቸውን ድምፅ በመፍጠር ሂደት ላይ ሙሉ ቁጥጥር ሊኖራቸው ይገባል፤ ምክንያቱም አፍሪካዊው የራሱን ታሪክ ያለምንም የውጭ ማሻሻያ በራሱ መንገድ መናገር ይችላልና። ሙዚቃው በሌላ አካል ሲዘጋጅ ግን፣ እንደምናውቀው፣ አንዳንድ የራሱ ክፍሎችን ሊያጣ እና ለሌሎች ፍላጎት ብቻ የተመቻቸ ሊሆን ይችላል።” ሲል ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ተጫዋች፣ አቀናባሪ እና ፕሮዲዩሰር ኪሩቤል አሰፋ ከበደ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል፡፡

በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የኢትዮጵያን ሙዚቃ እና የባህል ቅርስ ወደ ዓለም አቀፍ ለስላሳ ኃይል (Soft Power) እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ኢንዱስትሪ የመቀየር አቅም እንቃኛለን። ለዚህም፣ ከዓለም አቀፍ የጃዝ፣ የአፍሪካ እና የዘመናዊ ሙዚቃ ገበያዎች ጋር በመገናኘት ሰፊ ልምድ ካለው የሙዚቃ መሣሪያዎች ተጫዋች፣ አቀናባሪ እና ፕሮዲዩሰር ኪሩቤል አሰፋ ጋር ቆይታ አድርገናል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0