- Sputnik አፍሪካ, 1920
30 ሴኮንድ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር

ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን ቀድሞ ለመከላከል የምትተገብረው አዲሱ የጤና ሥርዓት

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን ቀድሞ ለመከላከል የምትተገብረው አዲሱ የጤና ሥርዓት

​በመረጃ ላይ የተመሠረተ የጤና ፖሊሲን እና የእቅድ አፈጻጸምን ለማሻሻል የሚያስችል "የጤና እና የዴሞግራፊክ ክትትል ሥርዓት" ተግባራዊ ልታደርግ ነው፡፡

ሥርዓቱ የሚከተሉት ፋይዳዎች ይኖሩታል

🟠 በሽታዎችን ቀድሞ መከላከል፦ እንደ ወባ ያሉ ወረርሽኞችን በቴክኖሎጂ በፍጥነት በመለየት መከላከል ያስችላል።

🟠 መድኃኒቶችን ቀድሞ ማቅረብ፦ ለየአካባቢው የሚያስፈልጉ መድኃኒቶችንና የሕክምና ቁሳቁሶችን ቀድሞ ለማድረስ ይረዳል።

🟠 በመረጃ የተደገፉ ፖሊሲዎችን ማውጣት፦ የሞት መንስኤዎችን በመመዝገብ ትክክለኛ የጤና ፖሊሲዎችንና ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ያመቻቻል።

🟠 የጤና ተቋማትን በፍትሃዊነት መገንባት፦ የሕዝብ ቁጥርና የጤና ችግር የበዛባቸውን ቦታዎች በመለየት አዳዲስ ግንባታዎችን ያመላክታል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የስፑትኒክ አፍሪካን ቪዲዮ ይመልከቱ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0