ሩሲያ እና ደቡብ አፍሪካ በአዲስ የመግባቢያ ሰነድ የኦሊምፒክ አጋርነታቸውን አሰፉ

ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ደቡብ አፍሪካ በአዲስ የመግባቢያ ሰነድ የኦሊምፒክ አጋርነታቸውን አሰፉ

የሩሲያ የስፖርት ሚኒስትር እና የሩሲያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ሚካኤል ዴግቲያሬቭ በቭላዲቮስቶክ በተካሄደው የምስራቃዊ ኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን ከደቡብ አፍሪካ ስፖርት ኮንፌዴሬሽን እንዲሁም የኦሊምፒክ እና ፓራሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ባሪ ሄንድሪክስ ጋር ተወያይተዋል።

ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች የጋራ ውድድሮችን እና የሥልጠና መርሃ ግብሮችን የሚያካተት የትብብር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፤ ከእነዚህም መካከል፡-

እግር ኳስ፣

ቼዝ፣

‍ዋና፣

መረብ ኳስ፣

ጂምናስቲክ፣

ቦክስ እና ኪክቦክሲንግ፣

ካራቴ፣

ፌንሲንግ (የሰይፍ ውጊያ ውድድር) እና ሌሎችም ይገኙበታል።

"በሁሉም ደረጃዎች የስፖርተኞቻችንን ህዋስ የመመለስ እና የማገገም ሂደት በተመለከተ ሁልጊዜም የደቡብ አፍሪካን ወዳጃዊ ድጋፍ እንገነዘባለን" ሲሉ ዴግቲያሬቭ ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0