በርካታ የቀድሞ አማፂያን የማሊ መከላከያ ሠራዊትን ተቀላቀሉ - መግለጫ
09:57 04.09.2026 (የተሻሻለ: 10:04 04.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በርካታ የቀድሞ አማፂያን የማሊ መከላከያ ሠራዊትን ተቀላቀሉ - መግለጫ
ከኪዳል የመጡ 37 የቀድሞ ተዋጋዮች በአኔፊስ ካምፕ ውስጥ በ7ኛው ወታደራዊ ክልል ዕዝ ፊት በይፋ ቃለ-መሐላ ፈጽመዋል ሲል የማሊ ሠራዊት ያወጣው መግለጫ አመልክቷል።
◻ ሰፊው የመቀላቀል ጥረት አካል፦ እርምጃው ሀገራዊው "ትጥቅ መፍታት፣ ማቋቋም፣ ዳግም መቀላቀል እና ውህደት" ማዕቀፍ አካል ነው።
◻ ስትራቴጂካዊ ዓላማ፦ የቀድሞ ተዋጋዮችን መልሶ በመቀላቀል ሰላምን ለማፅናት፣ ማኅበራዊ ትስስርን ለማጠናከር እና የሀገርን የመከላከያ አቅም ለማጎልበት ያለመ መሆኑን ባለሥልጣናቱ አፅንኦት ሰጥተውበታል።
◻ ለአገልግሎት ዝግጅት፦ አዲሶቹ ተመልማዮች ወታደራዊ ታክቲክን፣ የወታደርነት ትምህርትን እና የአካል ብቃት ስልጠናን ያካተተ የስድስት ወራት ፕሮግራም በብቃት አጠናቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X