የአርክቲክ አማራጭ፦ ሙሉ ዓመቱን የሚሠራ የሩሲያ የትራንስፖርት ኮሪደር ለአፍሪካ ምን ትርጉም ይኖረዋል?

© telegram sputnik_ethiopiaየአርክቲክ አማራጭ፦ ሙሉ ዓመቱን የሚሠራ የሩሲያ የትራንስፖርት ኮሪደር ለአፍሪካ ምን ትርጉም ይኖረዋል?
የአርክቲክ አማራጭ፦ ሙሉ ዓመቱን የሚሠራ የሩሲያ የትራንስፖርት ኮሪደር ለአፍሪካ ምን ትርጉም ይኖረዋል? - Sputnik አፍሪካ, 1920, 04.09.2026
ሰብስክራይብ

የአርክቲክ አማራጭ፦ ሙሉ ዓመቱን የሚሠራ የሩሲያ የትራንስፖርት ኮሪደር ለአፍሪካ ምን ትርጉም ይኖረዋል?

ሩሲያ በ"ትራንስ-አርክቲክ የትራንስፖርት ኮሪደር" በኩል የሚደረገውን የባሕር ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ዓመቱን ሙሉ እንዲሠራ ለማድረግ ያለመች ሲሆን፣ እስከዚህኛው አሥር ዓመት ማብቂያ ድረስ የሚያጓጉዘውን የጭነት መጠን ቢያንስ 70 ሚሊዮን ቶን ለማድረስ አቅዳለች ሲሉ ፕሬዝዳንት ቭላዲሚር ፑቲን በ2026ቱ የምስራቅ ኢኮኖሚ ፎረም ገልጸዋል።

ትራንስ-አርክቲክ የትራንስፖርት ኮሪደር ምንድን ነው?

"ትራንስ-አርክቲክ የትራንስፖርት ኮሪደር" በሩሲያ ሰፊ የትራንስፖርት መረብ ሲሆን፣ 'የሰሜን ባሕር መስመር' ደግሞ የዚህ መስመር ዋና የባሕር ክፍል ነው።

'የሰሜን ባሕር መስመር' በሩሲያ የአርክቲክ የባሕር ዳርቻ አቅጣጫ ወደ 5,600 ኪሎ ሜትር ያህል ይዘረጋል።

አሁን ላይ ለምንድነው የመርከብ ጉዞ ዓመቱን ሙሉ የማይሆነው?

የባህር በረዶ በቀዝቃዛዎቹ ወራት የመርከብ ጉዞን ይበልጥ አስቸጋሪ የሚያደርገው ሲሆን፣ የበረዶ መቋቋም አቅም ያላቸው መርከቦችን እና በረዶ ሰባሪዎችን ይፈልጋል።

ሩሲያ እንቅስቃሴው ዓመቱን ሙሉ እንዲቀጥል ለማስቻል የልዩ መርከቦች ስብስብን እና ተዛማጅ የመሠረተ ልማት አቅሟን እያሰፋች ትገኛለች።

አፍሪካ ከዚህ ጉዳይ ጋር እንዴት ትገናኛለች?

ከአፍሪካ ጋር ያለው ቁርኝት ከአርክቲክ በቀጥታ ወደ አፍሪካ በሚደረግ የዝውውር መስመር ሳይሆን፣ በሩሲያ ሰፊ የትራንስፖርት መረብ በኩል የሚፈጠር ነው፦

'የሰሜን ባሕር መስመር' በሩሲያ የአውሮፓ እና እስያ ክልሎች መካከል ያለውን የባሕር ትስስር ሊያጠናክር ይችላል።

በሌላ በኩል ደግሞ 'ዓለም አቀፍ የሰሜን-ደቡብ የትራንስፖርት ኮሪደር' ሩሲያን ከኢራን እና ከፋርስ የባሕር ሰላጤ ጋር ያገናኛል።

የሩሲያ ባለሥልጣናት ቀደም ሲል የሰሜን-ደቡብ ኮሪደርን ከአፍሪካ ጋር ለሚደረግ ንግድ፣ በአህጉሪቱ በሚገኙ የሎጂስቲክስ ማዕከላት በኩል መጠቀም እንደሚቻል ተወያይተውበታል።

እነዚህ የትራንስፖርት መረቦች እየሰፉ እና ከአፍሪካ የንግድ መስመሮች ጋር እየተጣመሩ ሲሄዱ፣ በሩሲያ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ እና በአፍሪካ መካከል ሰፊ የንግድ ትስስር እንዲፈጠር የመደገፍ አቅም ይኖራቸዋል።

አፍሪካ ከዚህ ምን ልታተርፍ ትችላለች?

እነዚህ ትስስሮች ከተረጋገጡ አፍሪካውያን ሀገራት የሚከተሉትን ጥቅሞች ሊያገኙ ይችላሉ፦

ከሩሲያ ጋር ለሚደረግ ንግድ ተጨማሪ የትራንስፖርት መስመሮችን፤

ሰፊ የትራንስፖርት አማራጮች ማግኘት፤

ለአፍሪካ የወደብ እና የሎጂስቲክስ ማዕከላት አዳዲስ የንግድ ዕድሎች፤

በአፍሪካ የትራንስፖርት መረቦች እና በሰሜን-ደቡብ ኮሪዶር መካከል ጠንካራ ትስስር መፈጠር፤

የአፍሪካ ምርቶች ወደ ሩሲያ ገበያ በቀላሉ የመግባት ዕድል።

ይህ ለአፍሪካ የሚኖረው አወንታዊ ተፅዕኖ በመጨረሻም የሚወሰነው እነዚህ የትራንስፖርት መስመሮች በተግባር የመልማታቸው እና የመገናኘታቸው ሁኔታ ላይ ይሆናል።

በሰው ሠራሽ አስተውሎት የተዘጋጀ ምስል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0