ሩሲያን በማዕቀብ ለማግለል የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታቸው የተገላቢጦሽ ነው - የሰርቢያ ባለስልጣን

ሰብስክራይብ

ሩሲያን በማዕቀብ ለማግለል የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታቸው የተገላቢጦሽ ነው - የሰርቢያ ባለስልጣን

​"ያለ ሩሲያ ኢኮኖሚ ዓለም በጣም ድሃ ትሆናለች" ሲሉ የቀድሞው የሰርቢያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ቩሊን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

​ በሩሲያ ቭላዲቮስቶክ ከተካሄደው የምስራቃዊ የኢኮኖሚ ፎረም ጎንዮሽ በሰጡት አስተያየት፤ የአውሮፓ የአስርተ ዓመታት ብልጽግና በርካሽ የሩሲያ ኃይል አቅርቦት የተደገፈ እንደነበር አውስተዋል።

​"አሁን ግን በዓለም ገበያ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ መክፈልን መርጠዋል። ለምን?" ሲሉ ጠይቀዋል።

​ አስተያየታቸው ሀገሪቱ የማዕቀብ ጫናዎችን መላመዷን የሚገልጹ የሩሲያ ባለሥልጣናት ተደጋጋሚ መግለጫዎችን ያስተጋባ ነው። በተመድ የሩሲያ ቋሚ መልዕክተኛ ቫሲሊ ኔቤንዝያ፤ ሞስኮ ለምዕራባውያን የኢኮኖሚ ማስፈራሪያዎች ብዙም ትኩረት እንደማትሰጥ እና "የትኛውንም ማዕቀብ እና ዛቻ መቋቋም ችለናል" ሲሉ በቅርቡ መናገራቸው ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0