- Sputnik አፍሪካ, 1920
Continental Drift
በአፍሪካ ቅርፅ እየቀየሩ ያሉትን እንደዚሁም የደቡባዊውን ዓለም ክፍል ሚና በአዲስ መልክ እየገለጹ ያሉትን ስር ነቀል ለውጦች የሚቃኝ ፕሮግራም ነው። ትዕይንቱ ፖሊሲዎች፣ ገበያዎች እና ፈጠራዎች ከዕለት ተዕለት ሕይወት ጋር እንዴት እንደሚገናኙ በመመርመር በእውነታ ላይ የተመሰረቱ ግንዛቤዎችን እና ትክክለኛ የአፍሪካ አመለካከቶችን ያቀርባል።

ዓለም ወደ ደቡባዊ ዓለምና ምሥራቅ እያዘነበለች ነው ፦ ለአፍሪካ ይዞት የሚመጣዉ ዕድል ምንድን ነው ?

ዓለም ወደ ደቡባዊ ዓለምና ምሥራቅ እያዘነበለች ነው ፦ ለአፍሪካ ይዞት የሚመጣዉ ዕድል ምንድን ነው ?
ሰብስክራይብ
የዓለም ኢኮኖሚ እየተለወጠ ነው። የኢኮኖሚ እና የንግድ ኃይል ከባህላዊ ማዕከላት በመውጣት ወደ እስያና ወደ ተለያዩ የዓለም ክልሎች እየተስፋፋ ነው። ሩሲያ የሩቅ ምሥራቅ ክልሏን ከእስያ-ፓሲፊክ ጋር ለማገናኘት እየሰራች ሲሆን፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ኢንዶኔዢያ እና ሌሎች የእስያ ኢኮኖሚዎችም በአዲሱ የዓለም ኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ የበለጠ ሚና እየወሰዱ ነው። ይህም እ.ኤ.አ ከመስከረም 1 እስከ 4 2026 በሩሲያ ቭላዲቮስቶክ - የምስራቃዊ ኢኮኖሚ ፎረም በሰፊው እየተነሳ ነው፡፡
በብዙ ማዕከላዊ የኢኮኖሚ ሥርዓት ተጠቃሚ ለመሆን፣ አገራት ራሳቸውን ወደ ዓለም ኢኮኖሚ ማዕከል ማምጣት አለባቸው፤ ይህም በመከፋፈል ሳይሆን በትብብር፣ በመቀናጀት እና በኢኮኖሚ ውህደት ሊሳካ ይችላል።” ሲሉ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ተመራማሪዉ ዱጋሳ ሙለጌታ(ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ ከቭላዲቮስቶክ እስከ አዲስ አበባ የሚዘልቀውን የዓለም ኢኮኖሚ ለውጥ፣ የሩሲያ ሩቅ ምሥራቅ ከእስያ ጋር እየገነባ ያለውን የኢኮኖሚ ትስስር እና የበርካታ የኢኮኖሚ ማዕከላት መፈጠር ለአፍሪካና ለኢትዮጵያ የሚያመጣውን ዕድል እንቃኛለን።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0