- Sputnik አፍሪካ, 1920
Continental Drift
በአፍሪካ ቅርፅ እየቀየሩ ያሉትን እንደዚሁም የደቡባዊውን ዓለም ክፍል ሚና በአዲስ መልክ እየገለጹ ያሉትን ስር ነቀል ለውጦች የሚቃኝ ፕሮግራም ነው። ትዕይንቱ ፖሊሲዎች፣ ገበያዎች እና ፈጠራዎች ከዕለት ተዕለት ሕይወት ጋር እንዴት እንደሚገናኙ በመመርመር በእውነታ ላይ የተመሰረቱ ግንዛቤዎችን እና ትክክለኛ የአፍሪካ አመለካከቶችን ያቀርባል።

የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዕድገት፡ የመንግስት ቁርጠኝነት እና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች

የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዕድገት፡ የመንግስት ቁርጠኝነት እና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እያሳየ ያለው ፈጣን ዕድገት እና የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ወሳኝ ማዕዘን ሆኗል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት ለዘርፉ የተሰጠው ልዩ ትኩረት እና የኢኮኖሚ ምሰሶ መሆኑ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ ሀገር አቀፍ የቱሪዝም መሠረተ ልማቶችን ለማጠናከር እና ባህላዊ እሴቶችን ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለማሸጋገር ትልቅ አቅም ፈጥሯል።

"ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ተነሳሽነት ጀምሮ ለቱሪዝም ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷል፤ ቱሪዝምም የኢኮኖሚው አምስት ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። ይህ ማለት ለዘርፉ ከፍተኛ በጀት እና ትኩረት ተሰጥቷል ማለት ነው። ኢትዮጵያ በፍጥነት ከሚያድጉ እና ከቀዳሚ የቱሪዝም መዳረሻዎች አንዷ እንድትሆን ካደረጓት ዋና ዋና ምክንያቶች አንዱ ይህ የመንግስት ቁርጠኝነት ነው።" ሲሉ የኢትዮጵያ ቱሪዝም እና ሆቴል ገበያ ማህበር ፕሬዚዳንት ጌታሁን አለሙ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

በዛሬው የ ኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የኢትዮጵያን ቱሪዝም ዘርፍ ፈጣን ዕድገት፣ የመንግስትን ቁርጠኝነት እና የኢኮኖሚ ምሰሶነቱን እንዲሁም እንደ እንቁጣጣሽ ያሉ ባህላዊ በዓላትን ወደ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ምርት መቀየር የሚቻልበትን ሁኔታ እንቃኛለን። ለዚህም የኢትዮጵያ ቱሪዝም እና ሆቴል ገበያ ማህበር ፕሬዚዳንት ጌታሁን አለሙ ጋር አድርገነውን ቆይታ እናቀርባለን።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple Podcasts – DeezerAfripodsSpotifyPocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0