ኢትዮጵያ 12 የጤና ባለሙያዎችን ወደ ባርባዶስ ላከች
19:01 02.09.2026 (የተሻሻለ: 19:04 02.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ 12 የጤና ባለሙያዎችን ወደ ባርባዶስ ላከች
ባለሙያዎቹ በባርባዶስ ሕጋዊ የሁለት ዓመት ኮንትራት ፈርመው ለሥራ እንደሄዱ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ኢትዮጵያ እና ባርባዶስ የጤና ባለሙያዎቹን የሥራ ሁኔታ እና የክፍያ ስምምነትን በተመለከተ የመንግሥት ለመንግሥት ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት የባለሙያ ፍልሰትን ለመምራትና የሥራ ዕድል ለማስፋት የሁለትዮሽ ትብብሩን እያጠናከረ ነው ሲሉ ሚኒስትር ደኤታዋ ጨምረው ገልጸዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X