የናይጄሪያ ኢኮኖሚያ እስከ 2030 የ1 ትሪሊዮን ዶላር ግቡን ለማሳካት የሚያስችለው ጥንካሬ ላይ ነው ተባለ
18:44 02.09.2026 (የተሻሻለ: 18:54 02.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ ኢኮኖሚያ እስከ 2030 የ1 ትሪሊዮን ዶላር ግቡን ለማሳካት የሚያስችለው ጥንካሬ ላይ ነው ተባለ
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ ዕድገት እ.ኤ.አ በ2026 ሁለተኛው ሩብ ዓመት የተፋጠነ ሲሆን እውነተኛ የሀገር ውስጥ ምርት በዓመት 4.43% አድጓል። ይህ ቁጥር እ.ኤ.አ ከ2025 ሁለተኛ ሩብ ዓመት 4.23% እና ከመጀመሪያው ሩብ ዓመት 3.89% ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል።
የዕድገቱ መሠረት የሰፋ ሲሆን በሁለተኛው ሩብ ዓመት 27 የኢኮኖሚ ንዑሳን ዘርፎች ከ3% በላይ እውነተኛ ዕድገት አስመዝግበዋል። ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ይህ ቁጥር 23 ነበር።
ይህ ጭማሪ በዋናነት በአምራች ዘርፎች የተመራ ነው። የዘርፉ ዕድገት ከ2025 ሁለተኛ ሩብ ዓመት 1.60% ወደ 3.24% አድጓል። የግብርና ዘርፍ ከ2.82% ወደ 4.39% አድጓል።
ለኢኮኖሚው ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው የአገልግሎት ዘርፍም ከዚህ ቀደም ከነበረበት 3.94% ወደ 4.60% አድጓል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት፤ ናይጄሪያ እ.ኤ.አ በ2026 ከአጠቃላይ የዓለም እውነተኛ ዕድገት በግምት 1.5% ያህል ድርሻ እንደሚኖራት በመተንበይ፤ ከዓለም አቀፍ የዕድገት አስተዋጽኦ አበርካቾች መካከል ከከፍተኛዎቹ 10 ሀገራት ተራ አሰልፏታል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X