ናሚቢያ በመረጃ ተጋላጭነት እና የሉዓላዊነት ስጋቶች ምክንያት የአሜሪካን የጤና ስምምነት ውድቅ አደረገች
10:06 02.09.2026 (የተሻሻለ: 10:14 02.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ናሚቢያ በመረጃ ተጋላጭነት እና የሉዓላዊነት ስጋቶች ምክንያት የአሜሪካን የጤና ስምምነት ውድቅ አደረገች
መንግሥት፤ የቀረቡት የዳታ ማጋራት እና የናሙና ልውውጥ አንቀጾች ከሀገሪቱ ብሔራዊ ሕግጋት ጋር የሚቃረኑ ናቸው ማለቱን ሚዲያዎች ዘግበዋል።
ናሚቢያ በተጨማሪም ስምምነቱ አሜሪካ ሰፊ እና ለብቻዋ የሕክምና መረጃ ማግኘት የሚያስችላት መሆኑን የተቃወመች ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ አሠራር በሕገ-መንግሥቱ የተጠበቀውን የግላዊነት መብት እና በሥነ-ህይወት ቁሳቁሶች ላይ ያለውን ሀገራዊ ሉዓላዊነት የሚጥስ ነው ብላለች።
ናሚቢያ በዋሽንግተን ዓለም አቀፍ የጤና ስትራቴጂ ሥር ለኤች.አይ.ቪ እና ለቲቢ ፕሮግራሞች የቀረበውን የ40 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ውድቅ በማድረግ ጋና፣ ዛምቢያ፣ ዚምባብዌ እና ደቡብ አፍሪካን ተቀላቅላለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X